Friday, March 6, 2015

የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታ

የኢትዮጵያ መንግሥትን የሚቃወሙ 6 የኦሮሞ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በድሎናል ሲሉ አማረሩ ። የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን ያልተፈታ ችግር እንደሌለና በተለይ በአባላት ላይ ይደርሳል ስለተባለው እንግልት ቦርዱ እንዳልሰማ ተናግረዋል ።
Büro des National Electoral Board of Ethiopia NEBE
ፓርቲዎቹ ከዚህ ቀደም ከተደረሰበት ስምምነት ውጭ አባላቶቻቸው እንደሚንገላቱ የበጀት ድጎማ እንደማይሰጣቸውና ለምርጫ ቅስቀሳ አመቺ የአየር ጊዜ እንደተነፈጉ ተናግረዋል ። ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን ያልተፈታ ችግር እንደሌለ ተናግረዋል። በጀትን በተመለከተ ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች በሙሉ በእኩል የሚካፈፈለው ገንዘብ ሰሞኑን እንደሚለቀቅ አስታውቀዋል ።ሁለቱንም ወገኖች ያነጋገረው የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል ።

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC

No comments:

Post a Comment