የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታ
የኢትዮጵያ መንግሥትን የሚቃወሙ 6 የኦሮሞ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በድሎናል ሲሉ አማረሩ ። የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን ያልተፈታ ችግር እንደሌለና በተለይ በአባላት ላይ ይደርሳል ስለተባለው እንግልት ቦርዱ እንዳልሰማ ተናግረዋል ።

ፓርቲዎቹ ከዚህ ቀደም ከተደረሰበት ስምምነት ውጭ አባላቶቻቸው እንደሚንገላቱ የበጀት ድጎማ እንደማይሰጣቸውና ለምርጫ ቅስቀሳ አመቺ የአየር ጊዜ እንደተነፈጉ ተናግረዋል ። ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የምርጫ ቦርድ ሃላፊ ግን ያልተፈታ ችግር እንደሌለ ተናግረዋል። በጀትን በተመለከተ ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች በሙሉ በእኩል የሚካፈፈለው ገንዘብ ሰሞኑን እንደሚለቀቅ አስታውቀዋል ።ሁለቱንም ወገኖች ያነጋገረው የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝሩን ልኮልናል ።
No comments:
Post a Comment