Tuesday, June 2, 2015

ከኬንያ ተጠልፈው የነበሩት ሁለቱ የኦብነግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ ናይሮቢ ተመለሱ

ግንቦት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአንድ ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች ከኬንያ ተጠልፈው ወደ ኢትዮጵያ ተወስደው የነበሩት አቶ ሱሉብ አብዲ አህመድና አቶ አሊ አህመድ ሁሴን ትናንት ምሽት
ኬንያ ናይኖቢ መግባታቸውን ለኢሳት ደረሰው መረጃ አመልክቷል።
ሁለቱ ከፍተኛ አመራሮች በምን ሁኔታ ወደ ናይኖቢ እንደተመለሱ የታወቀ ነገር የለም። የድርጅቱ የውጭ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አብድረህማን ሼህ ማህዲ የመሪዎቹን ወደ ናይሮቢ መመለስ አረጋግጠው፣ በምን ሁኔታ እንደተመለሱ ግን ድርጅቱ
መግለጫ እንደሚሰጥ ለኢሳት ተናግረዋል።
በኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅትና በኢህአዴግ መካከል ድርድር እየተካሄደ ነው ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፣ ከዚህ በፊት አንዳንድ የድርድር ሙከራዎች ቢደረጉም፣ በአሁኑ ሰአት የሚደረግ ምንም አይነት ድርድር የለም ብለዋል።
የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት አማካሪ አብዲኑር አብዱላሂ ፋራህ የኦብነግ መሪዎቹ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል እጃቸውን ለመንግስት መስጠታቸውን ገልጸው ነበር።
በሌላ ዜና ደግሞ ባለፉት 5 ቀናት በኢህአዴግ ወታደሮች የሚደገፉት የሶማሊ ክልል ልዩ ሚሊሺያ አባላት በኢትዮ- ሶማሊ ድንበር አካባቢ በሚኖሩ አርብቶ አደሮች ላይ በወሰዱት እርምጃ የሟችና ቁስለኞች ቁጥር ማሻቀቡን የደረሰን መረጃ
ያመለክታል።
አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ 35 ሲቪሎች መገደላቸውን ቢዘግብም፣ የኢሳት ምንጮች ግን የሟቾቹን ቁጥር ከ70 በላይ ያደርሱታል። በርካታ ቁስለኞች ህክምና እንዳያገኙ በኢህአዴግ ወታደሮች በመከልከላቸው ለከፋ ችግር መጋለጣቸውንም
የደረሰን ዜና ያመለክታል። ግጭቱ መዋጮ ከመሰብሰብ ጋር ተያይዞ መነሳቱን ኦብነግ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
በሌላ በኩል ደግሞ ከቀናት የተኩስ ልውውጥ በሁዋላ በደቡብ ክልል በሃመር ወረዳ አንጻራዊ ሰላም መስፈኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።
በርካታ አርብቶ አደሮች በመከላከያ ሰራዊት አባላት መገደላቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ ካለፉት 3 ቀናት ጀምሮ የተኩስ ድምጽ አለመስማታቸውን ገልጸዋል። አርብቶአደሮቹ ትናንት ጥቃት እንደሚፈጽሙ ማስጠንቀቂያ ልከው የነበረ ቢሆንም፣
ዲመካ ከተማና አካባቢዋ ሌሊቱን በሰላም አሳልፈዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባላትና ፖሊሶች በብዛት ተሰማርተው እንደሚገኙም ነዋሪዎች ይገልጻሉ።

Thursday, May 28, 2015

የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ለመሆን ሲወዳደሩ ከነበሩት እጩዎች መካከል የኢትዮጵያው የገንዘብ ሚኒስትር ሶፊያን አሕመድ ተሰናበቱ።

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እንደ አዲስ ስታንዳርድ ዘገባ እየተካሄደ ባለው ዓመታዊው የባንኩ የቦርድ ስብሰባ ላይ ነው ለፕሬዚዳንትነቱ ሲወዳደሩ ከነበሩት ስምንት ዕጩዎች መካከል የገንዘብ ሚኒስትሩ ሶፊያን አህመድ የሴራውሊዮኗን ሳሞራ ሚሸል ካማራን ተከትለው ሁለተኛው ተሰናባች ሆነዋል።
ቦርዱ እንደ አውሮፓያኑ አቆጣጠር ባለፈው ፌብሩዋሪ 11 ቀን አቢጃን በሚገኘው የባንኩ ዋና ጽህፈት ቤት ባደረገው ስብሰባ ባንኩን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት ኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስትርን ጨምሮ ስምንት ስዎች በእጩነት መቅረባቸው ይታወቃል።
ይህም የሆነው አቶ ሶፊያንና ሌሎቹ ዕጩዎች ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር በሩዋንዳ-ኪጋሊ በተካሄደው የባንኩ ስብሰባ ላይ ፕሬዚዳንት ለመሆን እንደሚፈልጉ ፍንጪ በማሳየታቸው ነበር።
ላለፉት አስር አመታት ባንኩን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የቆዩት ዶናልድ ካቤሩካ በዚህ ዓመት መጨረሻ ሥልጣናቸውን ይለቃሉ።
ጋዜጣው እንደዘገበው የተለያዩ አገር መንግስታት በእጩነት የቀረቡት ዜጎቻቸው እንዲመረጡ ቅስቀሳ ቢያደርጉም ፣ የኢህአዴግ መንግስት ግን ለአቶ ሶፍያን ቅስቀሳ አላደረገም። መንግስት ለአቶ ሶፍያን ቅስቀሳ ለማድረግ ለምን እንዳልፈለገ የገለጸው
ነገር የለም። አቶ ሶፍያን ለአፍሪካ ህብረት መወደዳራቸው በመጪው ጊዜ በስልጣን ላይ እንደማይቆዩ አመላካች ሆኗል

በምርጫ ቦርድ ውጤት የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ የግንቦት15ቱን ምርጫ መቶ በመቶ ማሸነፉ ከተገለጸ በሁዋላ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል። ምንጮች እንደገለጹት በርካታ ፊደል ቀመስ አባሎቹ ኢህአዴግ አሸነፍኩ
ያለበትን የድምጽ ልዩነት አልተቀበሉትም። ውጤቱን የሚቃወሙ የግንባሩ አባላት ” ህዝቡ ከእንግዲህ በሰላም መንግስት እቀይራለሁ የሚለው እምነቱ ተሟጦ የሃይል አማራጭን ብቻ እንዲመለከት ከማድረጉም በላይ፣ የሃይል አማራጭን
የሚከተሉ ሃይሎች በህዝቡም ሆነ በአለማቀፉ ማህበረሰብም የተሻለ ተቀባይነት እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል” በማለት ለድርጅቱ አስተያየታቸውን እየሰጡ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ተገኘ የተባለውን ውጤት ከመደገፍ አልፈው፣ ህዝቡ እንዴት ለተቃዋሚዎች ይህን ያክል ድምጽ ሊሰጥ ቻለ በማለት በቁጭት አስተያየት የሚሰጡ ደጋፊዎች መኖራቸውንም ምንጮች ገልጸዋል።
ኢህአዴግ እያሰባሰበ ባለው መረጃ ላይ እንደተገለጸው፣ አንዳንዶች ” ይህ ህዝብ ምን አይነት ልቡ የማይታወቅ ከሃዲ ህዝብ ነው! እንዴት ይሄን ሁሉ ልማት እያዬ ለተቃዋሚ ድምጹን ሊሰጥ ቻለ?” የሚል አስተያየት ሰንዝረዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫ ቦርድ ራሱ ባወጣው ሰሌዳ መሰረት የምርጫውን ውጤት መግለጽ የነበረበት ግንቦት21 ቢሆንም፣ የግንቦት20 በአልን ለማድመቅ እንዲረዳ በሚል ከእቅዱ በፊት እንዲገለጽ መደረጉን ምንጮችን ዋቢ በማድረግ
ዘጋቢያችን ገልጿል።
ኢህአዴግ በየክልሉ ከፍተኛ ወጪ የወጣበት የፌሽታ በዓላትን አዘጋጅቷል። ትናንት የገዢው ፓርቲ ደጋፊ አርቲስቶች ያዘጋጁት የኪነጥበብ ምሽት በብሔራዉ ቲያትር ተካሂዷል፡፡፡ በርካታ የፌዴራል የመንግስት መ/ቤቶች በተለያዩ ሆቴሎች
በዓሉን ለማክበር ጥሪ አስተላልፈዋል።
ምርጫ ቦርድ የኢህአዴግን አሸናፊነት ቢያውጅም መድረክ የተባለው የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ስብስብ የምርጫውን ውጤት አልተቀበለውም። ድርጅቱ ምርጫው አነስተኛ የሚባሉ መስፈርቶችን እንኳ ያላሟላ በማለት አጣጥሎታል። መድረክ
በአገሪቱ ውስጥ ያሉ ገለልተኛ የሚባሉ ሰዎች ተመርጠው መምርራ እንዲያካሂዱ ጠይቋል።
ሰማያዊ ፓርቲ ምርጫውን በተመለከተ ይህን ዜና እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ ያለው ነገር የለም። መንግስት የሰማያዊ ፓርቲ ደጋፊዎችን እያዋከበ በማሰር ላይ መሆኑ፣ ፓርቲውን አጣብቂኝ ውስጥ ሳይከተው አልቀረም። ሰማያዊ የምርጫውን
ውጤት ይቀበለዋል ተብሎ አይጠበቅም።
የአሜሪካ መንግስትና የአውሮፓ ህብረት ምርጫውን በተመለከተ በርካታ እጸጾችን አውጥተው ቢገልጹም፣ ከኢህአዴግ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንደማያቋርጡ አስታውቀዋል። የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ባወጣው መግለጫ ዲፕሎማቶች
በምርጫ ታዛቢነት እንዳይሰታፉ መከልከላቸው፣ ምርጫው አሳታፊ አለመሆኑንና የተለያዩ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች መታሰራቸውን በመግለጫቸው አመልክተዋል።
በምርጫው ሂደት ያጋጠሙ በርካታ አስገራሚ ክስተቶች ለኢሳት እየደረሱ ነው። ግንቦት12 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ ልዩ ቦታው ላንቻ ወይም ጠመንጃ ያዥ ነዋሪ የሆነ አንድ የ12 ዓመት ህፃን የኢህአዴግን የምርጫ መልዕክት ያየዘ
ፖስተር ከተለጠፈበት ግድግዳ ላይ ቀደሃል በሚል 6 ወር ተፈርዶበታል።
በአዲስ አበባ ችሎት በሚባል ቦታ አርብ ግንቦት 14 ቀን 2007 ዓ.ም ሁለት ማየት የተሳናቸው ወጣቶች ተይዘው ታስረዋል። ወጣቶቹ የተያዙት አንደኛው ሙሉ ሰማያዊ ልብስ ለብሶ በመውጣቱ በተፈጠረው አተካራ ነው። የአካባቢው
ሴት ካድሬ አንደኛውን ማየት የተሳነው ወጣት “ለምን ሰማያዊ ልብስ ለበስክ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ነሆይ?” በማለት ጥያቄ ስታቀርበለት፣ ጓደኛው “ምን አገባሽ ምንስ ብለብስ!” የሚል መልስ መስጠቱን ተከትሎ፣ ግለሰቧ በብስጪት
ለደህንነቶች ባስተላለፈችው ጥቆማ መሰረት ሁለቱም ወጣቶች በድንገት ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን እስከዛሬ ድረስ ታስረው ይገኛሉ።
መነን መሰናዶና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም ፀሃይ ጮራ ት/ቤት ውስጥ የሚገኙ ቁጥራቸው 20 መምህራንና 30 ተማሪዎች የሰማያዊና የአንድነት ፓርቲ አባላት ናቸው በሚል ዝርዝራቸው ለጸጥታ አካላት ተልዕኮ በልዩ ሁኔታ ክትትል እንዲደረግባቸው ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከምርጫ በፊት ትዕዛዝ ተላልፎ እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

Thursday, May 14, 2015

በቴፒ 5 ሰዎች ተገደሉ

በጋምቤላና ደቡብ ክልል ድንበር አካባቢ የሪ በምትባል ቀበሌ 7 ሰዎች በተገደሉ ማግስት ሌሎች 5 ሰዎች ደግሞ በቴፒ ከተማ እንድሪስ ቀበሌ ውስጥ ከሌሊቱ 8 ሰአት ላይ በጥይት ተደብድበው መሞታቸውን የአካባቢው ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል።
የአካባቢው ሰዎች እንደሚሉት ከሟቾቹ መካከል አባትና ልጅ ይገኙበታል። ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ ገዳዮቹ ፖሊሶች ናቸው። ነዋሪዎች እንደሚሉት ሰዎቹ ይተገደሉት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ አማጽያንን ያስጠጋሉ፣ ይደግፋሉ ተብለው ነው። ኢሳት ለከተማው ፖሊስ በመደወል ለማጣራት ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካም።
ኢሳት ከሶስት ቀናት በፊት “ከመስከረም ወር ጀምሮ በቴፒና አካባቢዋ ያለው ግጭት ተባብሶ በመቀጠሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ስጋት ላይ መውደቃቸውንም፣ በእየለቱ በከተማዋ ውስጥ የጥይት ድምጽ እንደሚሰማና በርካታ ቁጥር ያላቸው የሸኮ መዠንገር ነዋሪዎች እየፈለሱ ወደ ቴፒ ከተማ በመግባት ላይ መሆናቸውን ” ዘግቦ ነበር።
ነዋሪዎች ጸጥታውን የሚያስከብርልን ሃይል አጥተናል በማለት በተደጋጋሚ አቤቱታ ያሰማሉ።

Monday, May 4, 2015

የኢህአዴግ ከፍተኛ ካድሬዎች በድርጅታቸው ግራ ተጋብተዋል

ሚያዝያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ የተገደሉትን ኢትዮጵያውያንን ለመዘከር የወጣው ህዝብ ተቃውሞውን ወደ ኢህአዴግ መንግስት ካዞረ በሁዋላ፣ ገዢው ፓርቲ ተቃውሞውን ያስነሳው በአገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ
የሚታገለው ሰማያዊ ፓርቲ ነው በማለት የከፈተው ሰፊና አሰልቺ ፕሮፖጋንዳ የህዝቡን አመለካከት ሊቀይር አለመቻሉ ከፍተኛ ካድሬዎችን ስጋት ላይ ጥሎአቸዋል፡፡
በመስቀል አደባባይ የታየውን ህዝባዊ ቁጣ  ሰማያዊ ፓርቲ የቀሰቀሰው የመንደር ሁከት ለማስመሰል በስሩ በሚገኙ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በተደጋጋሚ ፕሮፖጋንዳ የሰራ ቢሆንም ፣ ፕሮፓጋንዳው ሕዝቡን ብቻ ሳይሆን የራሱን አባሎች ማሳመን አለመቻሉ ከፍተኛ
ካድሬዎችን ድንጋጤ ላይ ጥሎአቸዋል።
በአዲስአበባ አስተዳደር በተለያዩ የመንግስት ቢሮዎች  ይህንኑ የሕዝብ ተቃውሞ በማስመልከት ሰማያዊ ፓርቲ ያቀነባበረው መሆኑን በመግለጽ ሁኔታውን ለማውገዝ ታስቦ ሰሞኑን ተከታታይ ስብሰባዎች የተካሄዱ ቢሆንም አጥጋቢ ውጤት ሊገኝባቸው አልቻለም፡፡
በተለይ የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ጭምር ፍረጃው አሳማኝ አለመሆኑን በመጥቀስ ሕዝቡ በተለይ በመልካም አስተዳደርና በኑሮ ውድነት ችግሮች ውስጥ ሆኖ መቃወሙ የሚጠበቅ እንደነበር፣ ከሰማያዊ ፓርቲ ይልቅ ወደውስጣችን በመመልከት ችግሩን ካልቀረፍን
ከዚህም የባሰ ችግር ሊገጥመን ይችላል በሚል የተንጸባረቁ ደፈር ያሉ አስተያየቶች ያልተጠበቁ በመሆናቸው የመድረክ መሪ ካድሬዎችን ጭምር አስደንግጦአል፡፡

Monday, April 27, 2015

በስደት በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸሙትን አሰቃቂ ድርጊቶች የሚያወግዙ ሰልፎችንና የሻማ ማብራት ስነስርአቶች ተካሄዱ

ሚያዝያ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባሳለፍነው ሳምንት በሊቢያ፣ በደቡብ አፍሪካና በየመን በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የደረሰውን አሰቃቂ ግፍ የሚቃወሙ ሰልፎች፣ የሻማ ማብራት ስነስርአቶችና ጸሎቶች በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በእስያና
በአውስትራሊያ ተካሂዷል። በለንደን ሰኞ ሚያዚያ 19 ቀን 2007 ዓም በተካሄደው ከፍተኛ ተቃውሞ ኢትዮጵያውያን በወገኖቻቸው ላይ የደረሱትን በደሎች አጥብቀው ኮንነዋል። ጋዜጠኛ ወንድማገኝ ጋሹ በስፍራው ተገኝቶ እንዳለው እስከ አንድ ሺ የሚጠጉ
ኢትዮጵያውያን ከትራፋልጋር ስኩየር በመነሳት ወደ እንግሊዝ ፓርላማ አምርተዋል። በኒዉዚላንድ ኦክላንድ  የኢትዮጵያ ትንሳኤ መወያያ መድረክ ባዘጋጀዉ የሻማ ሥነስርዓት ላይ ኢትዮጵያኑ የሻማ ማብራት ሥርዓት  አካሒደዋል፡ ፡
በጃፓን ቶክዮ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም በደቡብ አፍሪካ ኢምባሲ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል።
በስዊዘርላንድ ጄኔቫ፣ በዙሪክ፣ በርን፣ ሴንት ጋለን፣ ባዝል፣በፈረንሳይ ፓሪስ፣ በሆላንድ አምስተርዳም፣ በአውስትራሊያ ፐርዝ ፣ በጀርመን ፍራንክፈርት ፣ በሉክሰንበርግ ፣በኖርዌይ አስሎ፡በግሪክየህሊና ጸሎት ተካሂዷል።
በሌላ በኩል ደግሞ መንግስት በሊቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በግብጽ እና በካይሮ በኩል ለማውጣት እንቅስቃሴ መጀመሩን ቢያስታውቅም፣ ወደ አገራቸው መመለስ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ትሪፖሊ ለሚገኘው የመንግስት ተወካይ ስልክ ደውለው ምላሽ
ማጣታቸውን ተናግረዋል። ግብጽ የሚገኘው ኢምባሲ የሚሰጠው የስልክ ቁጥር አይሰራም በማለት አቤቱታ እያቀረቡ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ የተካሄደውን የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ በቁጥጥር ስር ውለው ከነበሩት ከ1 ሺ በላይ ወጣቶች፣ አብዛኞቹ ተፈትው ከ150 ያላነሱት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፖሊስ አስታውቋል።
ፖሊስ ተቃውሞውን ያስነሱት ሰማያዊ ፓርቲና አንድነት ፓርቲዎች ናቸው ብሎአል። ሰማያዊ ፓርቲ የመንግስትን ክስ  ወዲያው ውድቅ ሲያደርገው፣ አዲሱ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ትዕግስቱ አወሉ አንዳንድ አባሎቻችን ከእኛ እውቅና ውጪ ሰልፍ ላይ
ተገኝተዋል ብለዋል።  አቶ ትእግስቱ 1 የብሔራዊ ም/ቤት አባላችንና ሌላ 1 ጸሃፊ ሰልፉ ላይ መገኘታቸውን ከፖሊስ የምርመራ ሪፖርት ላይ ተመልክቻለሁ ብለዋል። የአቶ ትእግስቱ ንግግር በኤፍ ሬዲዮኖች እንዲራገብ የተደረገ ሲሆን፣ ንግግሩ ብዙ የአዲስ አበባ
ነዋሪዎችን ማበሳጨቱ ታውቋል።
አዲሱ የአንድነት ፓርቲ የኢህአዴግ ተለጣፊ መሆኑን ከዚህ በላይ ማሳያ የለም በማለት የህዝብ አስተያየት በማሳባሰብ ዘጋቢያችን በላከው መረጃ ላይ ጠቅሷል።

Friday, April 10, 2015

The ruling Ethiopian People Revolutionary Democratic Front (EPRDF), which came to power in 1991 after a guerilla war against the bloody Mengistu Haille Mariam regime, holds total political sway. The coalition, which consists of four political parties, holds 499 out of the 547 national assembly seats.
To illustrate the country’s political intolerance, the government often refers to the opposition in derogatory terms like “chauvinists”, “narrow nationalists”, “secessionists” or simply “enemies”.
The Ethiopian government controls all spheres of life, from media to people’s daily lives. The main national broadcaster, Ethiopian Television, and most of the 10 radio stations, are owned by the government. Introduced in 1992 and giving the police sweeping powers to detain journalists without trial and shut down dissenting media outlets, Ethiopian media laws make the National Security (Amendment) Bill 2014 look like a legal walk in the park.
The ruling Ethiopian People Revolutionary Democratic Front (EPRDF), which came to power in 1991 after a guerilla war against the bloody Mengistu Haille Mariam regime, holds total political sway. The coalition, which consists of four...
ECADFORUM.COM
Like · Comment · 

Thursday, April 9, 2015

በዞን 9 ጸሃፊዎች ላይ ማስረጃ ሊቀርብ አልቻለም ተባለ

መጋቢት ፩(ሚያዝያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ብሉምበርግ ዞን 9 በመባል በሚጠሩት ወጣት ጸሃፊዎችና ጋዜጠኞች ላይ የመንግስት አቃቢ ህግ ጠንካራ ማስረጃ ለማቅረብ አለመቻሉን ጠበቃውን አቶ አምሃ መኮንንን በመጥቀስ ዘግቧል።
በሽብርተኝነት ወንጀል የተከሰሱት 6 የዞን ዘጠኝ እና 3  ጋዜጠኞች ላለፉት 10 ወራት በእስር ላይ ከቆዩ በሁዋላ፣ ፍርድ ቤቱ በቅርቡ ምስክሮችን የመስማት ሂደቱን ጀምሯል።  ይሁን እንጅ እስካሁን ባለው ሂደት የቀረቡት ምስክሮች ጸሃፊዎችና ጋዜጠኞች ተይዘው ቤታቸውና መስሪያ ቤታቸው ሲፈተሽ በታዛቢነት የነበሩ እንጅ ፣ ተከሳሾቹ በተለይም ክስ ከቀረበባቸው ከግንቦት7 እና ከኦነግ ጋር ግንኙነት እንዳላቸው የሚያመላክት ምስክር ሊቀርብባቸው አልቻለም።
አቃቢ ህግ 35  የሰው ምስክሮች አሉኝ ብሎ ለፍርድ ቤቱ ቢያስታውቅም ” ምስክሮችን አላገኘሁዋቸውም” በሚል ሰበብ እስካሁን ሊያቀርባቸው አልቻለም። አቃቢ ህግ ወንጀሉን ያስረዱልኛል የሚላቸውን የሰው ምስክሮች በመጪው ወር መጨረሻ እንዲያቀርብ ፍርድ ቤት ትእዛዝ አስተላልፏል።
በኢትዮጵያ ባለው የተበለሸ  የፍትህ ስርአት ዜጎች ዋስትና አጥተው በእስር እየተሰቃዩ ነው በማለት አለማቀፍ ድርጅቶች በተደጋጋሚ ክስ ያሰማሉ። እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በርካታ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲካኞችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በሽብር ወንጀል ተወንጅለው በእስር ቤት ይሰቃያሉ። መንግስት ከአለማቀፉ ማህበረሰብ እስረኞችን እንዲፈታ ተደጋጋሚ ጥሪ ቢቀርብለትም ፣ ለመፍታት ፈቃደኛ አልሆነም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በማእከላዊ እስር ቤት የሚገኙ በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ እስረኞችን ፣ መንግስት የይቅርታ ደብዳቤ እንዲፅፉ ለማግባባት እየሞከረ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። መንግስት የይቅርታ ደብዳቤ ከጻፉ እንደሚፈታቸው ቢገልጽም፣ የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት ግን ፣ በአብዛኛው ተከሳሾች ላይ በቂ ማስረጃ በመጥፋቱ መንግስት እስረኞቹ የሚጽፉትን ደብዳቤ እንደማስረጃ በመጠቀም በፍርድ ቤት ሊወነጅላቸው ያስባል። ከአዲስ አበባ እና ከተለያዩ ክልሎች የመጡ በርካታ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያን በማእከላዊ እስር ቤት በስቃይ ላይ ይገኛሉ።

በአዲስአበባ የኤሌክትሪክና ውሃ መቆራረጥ ተባብሶ ቀጥሎአል  

መጋቢት ፩(ሚያዝያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስአበባ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ እና የመጠጥ ውሃ መጥፋት ባሳለፍነው ሁለት ሳምንታት ተባብሶ መቀጠሉ ህብረተሰቡን ለተለያዩ ወጪዎችና እንግልት እየዳረገ መሆኑንና በዚህ ጉዳይ መንግስት የሚሰጠውን መግለጫ ማመን የማይችሉበት ደረጃ መድረሳቸውን ነዋሪዎች ገለጹ።
የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው ነዋሪዎች በተለይ ባለፈው ሳምንት እና በያዝነው ሳምንት የኤሌክትሪክ ኃይል ለረጀም ሰዓታት እንደሚጠፋ ተናግረዋል፡፡ በአዲስአበባ የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጡ በአንድ ጊዜ ድፍን ከተማዋን የሚሸፍን መሆኑና የሚቆበት ጊዜም ወደአንድ ሙሉ ቀን ወይንም ሌሊት መቀየሩ ደግሞ ግራ የሚያጋባ መሆኑ ታውቆአል፡፡
የመጠጥ ውሃ መቆራረጥም ከጊዜ ወደጊዜ ሊሻሻል ይችላል የሚል ተስፋ እንደነበራቸው ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ገልጸው፣  ነገርግን በአሁኑ ሰኣት ውሃ የማይኖርባቸው ቀናት እየጨመሩ መምጣታቸው አሳሳቢ እንደሆነባቸው ተናግረዋል፡፡ አንድ በካዛንቺስ አካባቢ በአነስተኛ ምግብ ቤት ንግድ የሚተዳደሩ ነዋሪ ውሃ የሚጠፋባቸው ቀናት በአሁኑ ወቅት በተከታታይ ለሶስትና ለአራት ቀናት እየሆነ መምጣቱ አስደንግጦናል ካሉ በኃላ፣  ኤሌክትሪክም ቢሆን ደጋግሞ መቆራረጡ ምግብ ለማብሰል ባለመቻላቸው ለተጨማሪ ወጪና ኪሳራ እየተዳረጉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡  አያይዘውም ውሃ መጣ ሲባል ኤሌክትሪክ እየጠፋ፣ ችግሩም ዕለት ከዕለት እየተባባሰ ኑሮአችንን እያመሰቃቀለ ነው ብለዋል፡፡
በተለይ ከኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ ጋር ተያይዞ በርካታ አገልግሎት ሰጪ መንግስታዊ መ/ቤቶች ስራ እየተደናቀፈ ከመሆኑም በላይ አምራች ኢንዱስትሪዎች የኤክስፖርት ትዕዛዝ ማሟላት አለመቻልና ሠራተኞቻቸውን እስከመቀነስ አድርሶአቸዋል፡፡ “በመንግስት በኩል ችግሩን እየፈታን ነው፣ አዳዲስ የውሃ ጉድጓዶች እየቆፈርን ነው፣ያረጁ የኤሌክትሪክ መስመሮችን በአዲስ እየቀየርን ነው” ከማለትና ተስፋ ከመስጠት ያለፈ ችግር ፈቺ መፍትሔ እየሰማን አይደለንም ያሉት ነዋሪዎቹ፣ አሁን አሁን ችግሩን ለመፍታት መንግስት አቅም እንደሌለው እየተረዳን በመምጣታችን ከንግግሮቻቸው ምንም ቁምነገር መጠበቅ ትተናል ብለዋል፡፡
ኢህአዴግ መራሹ መንግስት በአሁኑ ወቅት ከእነዚህ መሰረታዊ የህዝብ ችግሮች ይበልጥ የመጪው ምርጫ ጉዳይ እያሳሰበው በመሆኑ፣ ከምርጫው በፊት መፍትሔ የማግኘታቸው ነገር እንዳሳሰባቸውም ያነጋገርናቸው ወገኖች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ ከከተማው ሕዝብ ከ75 በመቶ በላይ 24 ሰኣታት ውሃ ያገኛል ሲሉ መግለጫ መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡

Tuesday, April 7, 2015

በአለማቀፍ ድርጅቶች እርዳታ ከአንድ መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ከየመን ወደ አገራቸው ተመለሱ

መጋቢት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅት _IOM ባወጣው ዘገባ ህይወታቸው በአደገኛ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 131 ኢትዮጵያውያንን ከጅቡቲ ወደ አገራቸው መልሷቸዋል።
ከተመላሾቹ መካከል 100 ያህሉ ኢትዮጵያውያ ወደ የመን ለመጓዝ በዝግጅት ላይ እንደነበሩ ድርጅቱ አስታውቋል። 28 ኢትዮጵያውያን ደግሞ ከየመን ወደ ጅቡቲ በባህር ላይ ጉዞ አድርገው የደረሱ ናቸው።
በሰላም ወደ አገራቸው ከተመሰሉት መካከል አንድ እርጉዝ ሴት እና 37 ወላጅ አልባ ታዳጊዎች እንደሚገኙበት ድርጅቱ ገልጿል።
አይ ኦ ኤም በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በየመን በሚካሄደው ጦርነት የተነሳ መውጫ አጥተው እየተሰቃዩ ነው  ብሏል። ከተለያዩ መንግስታት የቀረቡለትን ጥያቄዎች ግምት ውስጥ በማስገባት ድርጅቱ 11 ሺ የሚሆኑ የውጭ አገር ዜጎችን ከየመን ለማውጣት
እንቅስቃሴ እንደሚጀምርም አስታውቋል። አንዳንድ አገሮች በየመን ላይ ያየር ጥቃት ከምትፈጽመዋ ሳውዲ አረቢያ ፈቃድ እየጠየቁ ለተወሰኑ ሰአታት አውሮፕላን እየላኩ ዜጎቻቸውን ለማስወጣት ችለዋል።
የኢህአዴግ መንግስት ኢትዮጵያውያኑን የማስወጣቱን ሃላፊነት ለአይ ኦ ኤም ሳይሰጥ እንዳልቀረ ምረጃዎች ያመለክታሉ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሃኖም በቻይና የባህር ሃይል ሰራተኞች ድጋፍ ወደ አገራቸው የገቡ 30 ሰዎችን ” የመጀመሪያው ዙር ስደተኞች ወደ አገራቸው ገብተዋል” ብለው ከሳምንት በፊት ቢያስታውቁም፣ ከዚያ በሁዋላ መስሪያ ቤታቸው ያለው ነገር የለም።

ገዢው ፓርቲ የጦርነት ያክል ዘምቶብናል ሲሉ የኦፌኮ ሊቀመንበር ተናገሩ

መጋቢት ፳፱(ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመድረክ አባል የሆነው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊ/መንበር አቶ በቀለ  እንደተናገሩት በመጪው ምርጫ ለመሳተፍ ድርጅታቸው በኦሮምያ የተለያዩ አካባቢዎች እጩዎችን ቢያሰማራም፣ እጩዎቹ እየታሰሩና
እየተደበደቡ በመሆናቸው መድረክ ቀጣዩን ሂደት ለመወሰን እየተነጋገረ ነው።
አቶ በቀለ በሆድሩ ጉድሮ አባሎቻቸው ቅስቀሳ እንዳያደርጉ መከልከላቸውን፣ በሜታ ሮቢ  ከ50 ያላነሱ ወጣቶች መታሰራቸውን፣ በግንደበረት የወረዳው አስተዳደር ሽጉጥ በማውጣት  አባሎችን ማስፈራራታቸውን ፣ ግንጭ ላይ ጽ/ቤታቸው መሰበሩን እና ሌሎችንም
እየደረሱባችው ያሉትን ችግሮች ተናግረዋል። ምርጫ ቦርድም ሆነ ፖሊስ መልስ ሊሰጡዋቸው እንዳልቻሉ የገለጹት አቶ በቀለ፣ ጥቃቱና ዘመቻው የማይታገስ ከሆነ መድረክ ስለሚወስደው እርምጃ እየተነጋገረ ነው ብለዋል።
የፊታችን ግንቦት የሚደረገው ምርጫ አለማቀፍ ትኩረት አልሳበም። የአውሮፓ ህብረትም ሆነ የካርተር ማእከል ምርጫውን እንደማይታዘቡ ይታወቃል  ገዢው ፓርቲ አንጻራዊ የሆነ ፉክክር ከሰማያዊ ፓርቲ እና ከመድረክ ይገጥመዋል ተብሎ ቢጠበቅም፣ በድርጅቶች ላይ
የሚደረሰው ጫና ብዙዎች ነጻ ምርጫ ይካሄዳል ብለው ተስፋ እንዳይጥሉ አድርጓቸዋል።

Thursday, March 26, 2015

በኦሮሚያ እና ሌሎች አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ ችግር ት/ቤቶችን ከማዘጋት አልፎ ለስደት እየዳረገ ነው

መጋቢት ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በመቶ ሚሊየን በሚገመት ወጪ በታላቅ ፌሽታ እያከበረ የሚገኘው የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) አመራር በአንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች
ትምህርት ቤቶችን እስከማዘጋት የደረሰውን የመጠጥ ውሃ ችግር ሊታደግ ያልቻለ መሆኑን መረጃዎች ጠቆሙ፡፡
ከግብርና ሚኒስቴር የወጣ አዲስ መረጃ እንደሚያሳየው፣ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተው የመጠጥ ውሃ ችግር ሕዝብን ለከፍተኛ ችግር ከመዳረጉም አልፎ የመማር ማስተማር ስራ በማደናቀፍ ትምህርት ቤቶችን እስከማዘጋት ደርሷል።
የመጠጥ ውሃ ችግር ከገጠማቸው የኦሮሚያ አካባቢዎች መካከል በአርሲ ዞን በጎሎልቻ፣ መርቲ፣ .ዝዋይ፣ ዱግዳ፣ ሴሩና ደጁ ወረዳዎች፣ በምዕራብ አርሲ ዞን በሻላ ሲራሮና ሻሸመኔ ወረዳዎች፣ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን በሚደጋ፣ ቁምቢያ መዩ ወረዳዎች፣ በምስራቅ
ሸዋ ዞን በቦሰት ወረዳ እና በጉጂ ዞን በሊበንና ሰባቦሩ ወረዳዎች አስከፊ የተባለ የመጠጥ ውሃ ችግር ማጋጠሙን ሚኒስቴሩ አጋልጦአል፡፡
የመጠጥ ውሃ ችግሩ በተለይ በአርሲ ዞን በዝዋይ ዱግዳና በሴሩ ወረዳዎች፣ በጉጂ ዞን በሊበን ወረዳ ት/ቤቶችን እስከማዘጋት የደረሰ ችግር መከሰቱ ተረጋግጦአል፡፡ በእነዚህ አካባቢዎች የተከሰተውን የመጠጥ ውሃ ችግር ለመቅረፍ ሚኒስቴሩ ከአጋር ድርጅቶች
ባገኘው ድጋፍ ውሃ በቦቴ የማደል ስራ እያከናወነ መሆኑ ታውቋል፡፡
በቦረና ዞን አንዳንድ ወረዳዎች ማለትም በአሬሮ፣ ድሬ፣ ዲሎ፣ ዳስ የእንስሳት መዳከምና ሞት መከሰት የጀመረ ሲሆን በአርሲና ምዕ/ሐረርጌ ዞኖች የእንስሳቱ አቋም እየተዳከመ መሆኑ፣ የእንስሳት እንቅስቃሴም ተጀምሮ በምዕ/ሐረርጌ ዞን ከቡርቃ ዲምቱና ሃዊ
ጉዲና ወደ ዱንገታና ዋቤ ወንዝ፣ በቦረና ዞን ከተልተሌ ወደ ገራንና ኮንሶ፤ ከድሬ፤ ሚዮና ሞያሌ ወደ ኬንያ (አዋሳኝ ቦታዎች) በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸው በሪፖርቱ ተመልክቷል።
የኦሮሚያ ክልል ገዥ ፓርቲ ኦህዴድ/ኢህአዴግ  እንዲህ ዓይነቱን የህዝብ ችግር ሳይፈታ ለክብረበአል በመቶ ሚሊየን ብሮችን ሲያፈስ መታየቱ አሳዛኝ መሆኑን ዘጋቢያችን ያነጋገርናቸው የኦሮሞ ተወላጆች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
በአማራ ክልል ደግሞ በሰ/ሸዋ ዞን በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ፣ በሰ/ጎንደር ዞን በምስራቅ በለሳ ወረዳ በእያንዳንዳቸው 3 ቀበሌዎች የውሃ እጥረት፣ በዋግኸምራ ዞን በሳህላ፣ ዝቋላና ሰቆጣ ወረዳዎች፣ በሰ/ወሎ ዞን በላስታና ቡግና ወረዳዎች፣ በደ/ወሎ ዞን በመቅደላ
ወረዳ በ4 ቀበሌዎች፣ በኦሮሚያ ዞን በአ/ፉርሲ ወረዳና በምስ/ጎጃም ዞን ቆላማ አካባቢዎች የውሃ እጥረት ተከስቷል።
በሀረሪ ክልል በ5 ቀበሌዎችና በድሬዳዋ አስተዳደር ቆላማ ቀበሌዎችም ተመሳሳይ ችግር ተከስቷል። ችግሮችን ለመቅረፍ ውሃ በቦቴ ለማደል ሙከራ መደረጉም በሪፖርቱ ተጠቅሷል።

Wednesday, March 25, 2015

የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክቶች በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን እንዳይተላለፉ እየተደረገ ነው

መጋቢት ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን መጋቢት 16/2007 ዓ.ም ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ፣ ከተላኩት የቅስቀሳ መልክቶች መካከል ” የመከላከያ ሰራዊቱ ሌሎችም የአገሪቱ ቁልፍ ተቋማት ከገዢው ፓርቲ ካድሬዎች
ውጪ አልሆነም፣ በተለይም በገዛ ሃገራቸው ከስራ ይባረራሉ ፣ ተቋማቱን እውቀት የሌላቸው ካድሬዎች እንዲመሩት ተደርጓል፣ ገዢው ፓርቲ ፖሊስን፣ ሚዲያውን፣ መከላከያ ሰራዊቱን፣ ደህንነቱን ሰማያዊንና ሌሎች ተቃዋሚዎችን ለማጥፋት ሲጠቀምባቸው ቆይቷል
የሚሉትና ሌሎችም በህገ መንግስቱ የተቋቋሙ የዲሞክራሲ ተቋማትን ህልውና የሚክድና ተግባራቸውን የሚያንቋሽሽ መልእክቶች በመሆናቸውና ህገመንግስቱን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ስነምግባር ህጉን እና የድርጅታችንን ኢዲቶሪያል ፖሊሲ የሚጻረሩ ሆነው
ስለተገኙ አይተላለፉም ብሎአል።
ሰማያዊ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ መልዕክቶቹ እንዳይተላለፉ ሲከለከል የአሁኑ ለ8ኛ ጊዜ ነው፡

ኢህአዴግ የህዝቡ ብሶት አደጋ እንደሚያስከትል አውቋል” ስትል የአዲስ አበባ የኢህአዴግ የሴቶች ሊግ ም/ል ሊቀመንበር ተናገረች

መጋቢት ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሊጉ ም/ል ሊቀመንበር በመሆን ለአመታት ያገለገለችው ወ/ት እየሩሳሌም  አበረ  ከኢሳት ጋር ባደረገችው ቃለምልልስ “የአዲስ አበባ ህዝብ እንደሚገነፍል ድስት እፍ እፍ እየተባለ  ቢያዝም፣ አሁንም
በርካታ የዲሞክራሲ እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን እያነሳ ነው” ብላለች።
የታፈነ የመልካም አስተዳደር እና የዲሞክራሲ ጩኸት አለ የምትለው ወ/ት እየሩሳሌም፣ ገዢው ፓርቲም ህዝቡ በከፍተኛ ብሶት ላይ እንደሚገኝና አደጋ ሊያስከትል እንደሚችልም ጠንቅቆ ያውቀዋል ብላለች።
ከምርጫ 97 በሁዋላ ኢህአዴግ የተሳካለት ነገር ቢኖር ተቃዋሚዎችን ማፈን ነው የምትለው ኢየሩሳሌም፣ ህዝቡ በሚታየው ነገር ሁሉ ባለመርካቱ ገዢው ፓርቲ ቁጥጥሩን በማጥበቅ የህዝቡን ብሶት ለማፈን ይሞክራል ስትል አክላለች።
ወ/ት እየሩሳሌም ድርጅቱን ጥላ ስደትን መርጣለች። ለረጅም አመታት የአዲስ አበባ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ እና በሌሎችም የስልጣን ሃላፊነቶች ላይ ሲሰሩ የቆዩት የኦህዴድ ድርጅት አባል የሆኑት ወ/ሮ አበባ ገብረስላሴም በቅርቡ ኢህአዴግን በመተው፣ በአሜሪካ
ጥገኝነት ጠይቀዋል። ከወ/ት እየሩሳሌም ጋር የተደረገው ቃለምልልስ ሰሞኑን ይቀርባል።

Tuesday, March 24, 2015

ኢትዮጵያ የአባይ ግድብ ግንባታን በየደረጃው የሚቆጣጠረውን ስምምነት ፈረመች

መጋቢት ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ በጋራ የፈረሙት አዲሱ ስምምነት ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ በሙሉ ነጻነት የምትሰራውን ስራ እንደሚገድብ ከአረብኛ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመው  ሰነድ አመልክቷል።
ሰነዱ ኢትዮጵያ ግድቡን ለመገንባት በምታደርገው ማንኛውም እንቅስቃሴና በየትኛውም የግንባታ ደረጃ ላይ አለማቀፉ አጥኝ ቡድን ለሚሰጠው አስተያየት ተገዢ በመሆን እንድትተገብር ይገልጻል። አጥኝ ኮሚቴው የግድቡ ግንባታ የግብጽንና ሱዳንን የውሃ ድርሻ መጠን
ይቀንሳል ወይም በግብጽና ሱዳን አካባቢያዊ ሁኔታ ላይ ተጽአኖ ያመጣል የሚል ድምደማ ላይ ከደረሰ ካሳ እስከመክፈል የሚያደርስ ግዴታም መጣሉ ተመልክቷል።
አጥኚ ቡድኑ የመጨረሻውን የጥናት ውጤት ይፋ ካደረገ በሁዋላ ሶስቱም አገራት እንደሚቀበሉት የተስማሙ ሲሆን፣ ምናልባት አጥኝ ቡድኑ ግድቡ በግብጽና ሱዳን ላይ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግር ያስከትላል ብሎ ቢወስን ኢትዮጵያ የግድቡን ቅርጽ እስከመቀየር ልትደርስ ትችላለች።
ኢትዮጵያ የምትገነባው ግድብ፣ ከግብጽና ሱዳን የውሃ ማጠራቀሚያዎችን የሚጎዳ ከሆነም ኢትዮጵያ አገራቱን ፈጥና የማሳወቅና ለውጥ ማድረግ እንደሚኖርባትም ስምምነቱ ይገልጻል።
የስምምነቱ አብዛኛው ክፍል ኢትዮጵያ ስለምትፈጽማቸው ግዴታዎች ትኩረት ያደረገ ነው። ግብጽና ሱዳን ለአባይ ወንዝ የሚያበረክቱት የውሃ ድርሻ ካለመኖሩ አንጻር ስምምነቱ በዋነኝነት ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን መብት የሚገድብ ብቻ ሳይሆን፣ የአባይ ግድብ
ግንባታ እጣ ፋንታን ከኢትዮጵያ እጅ አውጥቶ በአለማቀፍ አጥኚዎች እጅ እንዲሆን የሚያደርገው ነው በሚል ትችት እየቀረበበት ነው።
ይሁን እንጅ ሶስቱም አገራት ስምምነቱን በማወደስ ለተግባራዊነቱ እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

Tuesday, March 17, 2015

የውሃና ችግር የኢትዮጵያውያን የዕለት ተዕለት መነጋገሪያ ሆኗል

መጋቢት (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለኢሳት የሚደርሱት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የንጹህ የመጠጥ ውሃ ችግር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ከትግራይ እስደ ደቡብ ክልል የውሃ ጀሪካኖችን በምንጮችና በውሃ መስጪያ ባንቧዎች ተሰልፈው ማየት የተለመደ ነገር ሆኗል። በዋና ከተማዋ አዲስ አበባም እንዲሁ በተለያዩ ቦታዎች የውሃ እጥረት ማጋጠሙን የየክልሉ ሪፖርተሮች ከሚልኩት እለታዊ መረጃ ለመረዳት ይቻላል።

የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት  በአሜሪካ የደረሰባቸው ተቃውሞ በጠ/ሚ ሃይለማርያም፣ ጌታቸውን አሰፋ፣ ኢሳትና ሌሎች ሃይሎች የተቀነባበረ ነው አሉ

መጋቢት (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በአንድ ኢትዮጵያዊ ከፍተኛ ተቃውሞ ያገጠማቸው አቶ አብዲ ሙሃመድ ተቃውሞውን ያቀነባበሩት ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ የደህንነት ሹሙ ጌታቸው አሰፋ፣ ኢሳት ፣ ግንቦት7 እና የኤራትራ መንግስት በጋራ በመሆን ነው ሲሉ አካራ ኒውስ በተባለው የግል ዌብሳይታቸው ላይ በሶማልኛ ባወጡት ረጅም ጽሁፍ ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ተቃውሞውን ሲያሰማ የነበረውን መኮንን የተባለውን ሰው ስም ከፊት በማስቀደም፣ መኮንን ጌታቸው አሰፋ ሃይለማርያም ብለው ጽሁፋቸውን ይጀምሩና  ኢሳት ከጀርባ ሆኖ ሲያቀናብር እንደነበር ያትታሉ።
የተቃውሞው እቅድ መክሸፉን የሚገልጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ኢሳት ቴሌቪዥንም ፕሬዚዳንቱ ሲናገሩት የነበረውን ንግግር ጥሩ ቢሆንም ሆን ብሎ እንዳይተላለፍ ያደረገው፣ እቅዱ መክሸፉን በመረዳቱ ነው ብለዋል።
በወጣው ጽሁፍ ዙሪያ አስተያየቱን የጠየቅነው በአንድ ወቅት የፕሬዚዳንት አብዲ የግል አማካሪ፣ የሶማሊ ክልል ወጣቶች ፕሬዚዳንትና የዚህ ዌብሳይት መስራች የሆነው፣ በአሁኑ ጊዜ በስዊድ አገር በስደት ላይ የሚገኘው ሰብአዊ መብት ተማጓቹ ወጣት አብዱላሂ ሁሴን ፣ አካራ ኒውስ በፈረንጆች አቆጣጠር በ2009 በፕሬዚዳንቱ ትእዛዝ መከፈቱንና እርሱ የውብሳይቱ ሃላፊና መስራች ሆኖ መስራቱን  ገልጿል። ዌብሳይቱ ለልዩ ሚሊሺያ ከተመደበው የመንግስት በጀት ተቀንሶ መቋቋሙን የሚገልጸው አብዱላሂ፣ በዌብሳይቱ ላይ ለሚሰሩ ጋዜጠኞች ገንዘብ የሚከፈለውም ከክልሉ ባጀት መሆኑን ይናገራል።
አብዱላሂ ዌብሳይቱን ሲመራ በነበረበት ወቅት ያገኛቸውን ቁልፍ የቪዲዮ ማስረጃዎች በመያዝ ከአገር ከወጣ በሁዋላ፣ ዌብሳይቱ በፕሬዚዳንቱ ታናሽ ወንድም በከድር ሙሃመድ ኡመር ስም እንዲመዘገብ መደረጉን አስረድቷል። በውብሳይቱ ላይ የሚወጣውን ማንኛውንም ጽሁፍ በቃል እየተናገረ የሚያስጽፈው ፕሬዚዳንቱ መሆኑን አብዱላሂ ገልጿል።
አቶ አብዲ፣ የደህንነት ሹሙ አቶ ጌታቸው አሰፋና ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ ተቃውሞውን አቀነባብረውታል ብሎ እንደሚያምን የገለጸው አብዱላሂ ምክንያቱ ደግሞ ከወራት በፊት ከተፈጠረው ክፍፍል ጋር ይያያዛል ብሎአል። የክልሉ የምክር ቤት አባላት 7 ለ5 በመወሰን አቶ አብዲን ከስልጣን ለማውረድ ሙከራ ቢያደርጉም፣ አቶ አብዲ ሀረር በሚገኙት በወዳጃቸው በጄኔራል አብራሃ አማካኝነት በስልጣን ላይ እንዲቆዩ መደረጉን አስታውሷል።
7ቱ የምክር ቤት አባላት አሁንም ተሰደው አዲስ አበባ እንደሚገኙ የሚገልጸው አብዱላሂ፣ በአቶ ሃይለማርያምና በአቶ ጌታቸው አሰፋ እንደሚደገፉም ገልጿል። አቶ አብዲ ለአቶ ሃይለማርያም ከፍተኛ ንቀት ያላቸው ሲሆን፣ ከእርሳቸው የሚመጣውን ትእዛዝ አይቀበሉም። አቶ አብዲ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ሰላም እንደሆኑ ለማሳየት ሁለቱ ሰዎች ጎን ለጎን ቁጭ ብለው የሚያሳይ ፎርጅድ ፎቶግራፍ አሰርተው በዚሁ ዌብሳይት ላይ እንዲወጣ ካደረጉ በሁዋላ፣ በደረሰባቸው ነቀፋ እንዲነሳ አድርገዋል።
በአቶ አብዲ ጉዳይ በአንድ በኩል የደህንነት ሹሙና አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የመከላከያው ሹም ጄኔራል አብርሃ ተፋጠው እንደሚገኙ የሚገልጸው አብዱላሂ፣ እስካሁን ባለው ሂደት መከላከያ በማሸነፉ እነ አቶ ሃይለማርያም ምንም ለማድረግ ሳይችሉ ቀርተዋል ብሎአል።
ፕሬዚዳንቱ ወደ አገር ሲመለሱ ችግር አይገጥማቸውም ወይ ተብሎ ለተጠየቀው ሲመልስ ደግሞ፣ የመከላከያ ባለስልጣናት እጃው ውስጥ እስካሉ ድረስ ምንም እንደማይሆኑ ይናገራል። ነገሮች ገፍተው ከመጡም ውብሳይቱ የእኔ አይደለም ሊሉ እንደሚችል አክሏል።
በመከላከያ አዛዦችና በአቶ አብዲ መካከል ያለው ግንኙነት ከግል ጥቅም ጋር የተሳሳረ መሆኑንም አብዱላሂ ይናገራል ። አቶ አብዲ ከኦብነግ ጋር የሚደረገው ድርድር ስልጣኔን አደጋ ውስጥ ይጥለዋል በሚል ስጋት አይቀበሉትም።
የአካራ ኒውስ ውብሳይት መተዳዳደሪያ ጽሁፍ እንደሚያሳየው ፣ ዌብሳይቱ ስለሶማሊ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ከባለስልጣኖች አንደበት የሚነገረውን እየተቀበለ እንደሚያሰራጭ ያትታል። በዌብሳይቱ ውስጥ የክልሉ ፕሬዚዳንት የሚያደርጉዋቸው እንቅስቃሴዎችና የአሜሪካ ጉብኝታቸው በፎቶ ተደግፎ ቀርቧል።
በተመሳሳይ ዜና ደግሞ አቶ አብዲ በሚኒሶታ ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሞቻዋል። በተቃውሞው ላይ  የሶማሊ ተወላጆች ኢትዮጵአውያንና ሌሎች ኢትዮጵያውያን በአንድነት በመሆን አቶ አብዱላሂ እናቶችን የሚገድል፣ ጨፍጫፊ፣ ገዳይ የሚሉ የተቃውሞ ድምጾችን አሰምተዋል
የሶማሊክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ሙሃመድ ኡመር እና በክልሉ የካቢኔ አባሎች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት ተከትሎ በጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጽ/ቤት በተካሄደው አስቸኳይ ግምገማ ፣ ፕሬዚዳንቱ ፈጸሟቸው የተባሉ በርካታ ወንጀሎች ተዘርዝረው ቀርበዋል።
ባለፈው ነሃሴ ወር አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በሰብሳቢነት በመሩት ግምገማ ላይ ም/ል ጠ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የጠ/ሚኒስትሩ የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ አለቃ ጸጋየ በርሄ፣የደህንነትምክትልሹሙኢሳያስ ወጊዮርጊስ፣የምስራቅእዝዋናአዛዥጄኔራልአብርሃበቅጽልስማቸውኳታር፣የፌደራልፖሊስወንጀልመከላከልሃላፊ ጄ/ልግርማየመንጁስ፣አቶአዲሱለገሰ፣አቶአብዲመሃመድናየተለያዩየክልሉየካቢኔአባላትእንዲሁምሌሎች 2 የኢህአዴግከፍተኛአመራሮችም በተገኙበት
አቶ አብዲ መገምገማቸውን ኢሳት ዘግቦ ነበር።
አቶአብዲስልጣንከያዙጀምሮእሳቸውበሚመሩትሚሊሺያበብዙመቶዎችየሚቆጠሩሰዎችበተለያዩምክንያቶችመገደላቸውን፣በርካታ ሲቪሎችታስረውህክምናሳይገኙበቀላፎ፣በፌርፌርናበሌሎችምእስርቤቶችእንዲሞቱ
ማደረጋቸቸውን፣ ከመንግስት የተመደበውን ግዙፍ በጀት ለአንዳንድ የፌደራል ባለስልጣናት በተለይም ለጄ/ልአብርሃ ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ በተለያዩ ወቅቶች እንዲሰጣቸው በማድረግና በተለያዩመንገዶች ከፍተኛ
ገንዘብእንዲዘርፍማድረጋቸው፣ የአገርሽማግሌዎችንበመሰብሰብ በአንቀጽ 39 መሰረትየራሳችንንመንግስት ስለምናውጅለዚህታሪካዊክስተትራሳችሁንአዘጋጁ፣ፌደራልመንግስትምበውስጥጉዳያችንጣልቃመግባትአይችልምብለውመናገራቸው፣
የልዩ ፖሊስ አባላትና የጎሳ አባላሎቻቸው ከፍተኛ ገንዘብ እንዲዘርፉ ማሰማራታቸው ፣በክልሉ የሚካሄዱትንትላልቅፕሮጀክቶችያለጫራታበመስጠትሆንብለውለብዝበዛአዘጋጅተዋልየሚሉ የግምገማ ነጥቦች ቀርበውባቸው ነበር።
በግምገማውወቅትጄ ልአብርሃበአቶአብዲላይየቀረበውንግምገማአጥብቀውመቃወማቸው ለአቶ አብዲ የስልጣን እድሜ መራዘም አስተዋጽኦ ማድረጉ በወቅቱ ተዘግቧል።

Monday, March 16, 2015

የኦሞ ስኳር ፕሮጀክቶች ግጭቶችን ሊያስከትሉ እንደሚችሉ አለማቀፉ ቡድን አስጠነቀቀ

የተለያዩ የአለም አገራትን፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን፣ የአፍሪካ ልማት ባንክንና ለጋሽ ተቋማትን ጨምሮ27 አባላትን የያዘውዲቨሎፕመንት አሲስታንስ ግሩፕ የተባለ አለማቀፍ ቡድን፤ በደቡብ ኦሞ በመከናወን ላይየሚገኙ ሰፋፊ የመንግስት የስኳር ፕሮጀክቶች በአካባቢውግጭቶችን ሊቀሰቅሱ እንደሚችሉ ባለፈው ረቡዕማስጠንቀቁን ብሉምበርግ ዘገበ፡፡
የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር / ሽፈራው ተክለ ማርያም በበኩላቸው፤ በደቡብ ኦሞ የሚከናወኑ የልማትስራዎች ግጭትን ለመከላከል ያለሙእንደሆኑና በአካባቢው የሚኖሩ ማህበረሰቦችም የልማት ዕቅዶቹንበተመለከተ በቂ ግንዛቤ እንዲይዙ ለማስቻል በስፋት መሰራቱን ከብሉምበርግጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅተናግረዋል፡፡ 
የስኳር ኮርፖሬሽን ከቻይና ልማት ባንክ ባገኘው ብድር በደቡብ ኦሞ አካባቢ ስድስት የስኳር ፋብሪካዎችንለመገንባትና 150 ሺህ ሄክታር ላይየሸንኮራ አገዳ ልማት ለማከናወን እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ የጠቆመውዘገባው፣ የሸንኮራ አገዳ ልማቱ የአካባቢውን ነባር ነዋሪዎች አኗኗርሊያቃውስ ይችላል ተብሎ እንደሚሰጋ ቡድኑማስታወቁን ገልጧል፡፡

Sunday, March 15, 2015


አደባባይ በመውጣት ሀሳባቸውን በመግለጽ ተለይተው የሚታወቁት ዳኛቸው በዩኒቨርስቲው ለሰባት ዓመታት አስተምረዋል፡፡ ዶክተሩ በአደባባይ በሚያደርጓቸው ተሳትፎዎች ደስተኛ ያልነበሩት ህወሓቶች ለዳኛቸው በሚቀርቧቸው ሰዎች አማካኝነት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ካልሆነም አገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ሲወተውቷቸው ቆይተዋል፡፡
ከወራት በፊት በዩኒቨርስቲው የሚያቆያቸውን ኮንትራት ለመፈረም ሲንቀሳቀሱ ዶክመንታቸው ከዩኒቨርስቲው መዝገብ ክፍል ተፈልጎ መጥፋቱ ሰዎቹ ሊያባረሯቸው እንደወሰኑ ፍንጭ እንደሰጣቸው በወቅቱ መናገራቸው አይዘነጋም፡፡
በዩኒቨርስቲው ለሰባት ዓመታት ላስተማሩ መመህራን የሚሰጠው የእረፍት ጊዜ ተፈቅዶላቸው እረፍት ለመውጣት ሲጠባበቁ በብጣቂ ወረቀት መሰናበታቸው እንደተነገራቸው የሚገልጹት ዳኛቸው ‹‹አሁን ገና ኢትዮጵያዊ መሆኔን አወቅኩ ምክንያቱም መበቴ ተረገጠ››በለዋል፡፡
ዶክተር መረራ ጉዲና ትናንት ምሽት በተላለፈው የምርጫ ክርክር ወቅት‹‹ኢህአዴግ ምሁራንን አይወድም››በማለት መናገራቸውን የሚያስታውሱ የዳኛቸው ስንብት መንስኤ ምን እንደሆነ በደንብ ይገነዘቡታል፡፡
Like ·  · 

Friday, March 13, 2015

አርሶ አደሮች ገንዘባችንን ተቀማን አሉ

መጋቢት ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል በባህር ዳር ከተማ በብአዴን አመራሮች እና በግንባር ቀደም አርሶ አደሮቸ ላለፉት አምስት አመታት የወረቀት ፈብሪካ ለመገንባት በሚል ከተሸላሚ አርሶ አደሮች የተሰበሰበው በሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ የት እንደገማ እንደማይታወቅ አርሶ አደሮች ተናግረዋል። ገንዘባቸው እንዲመለስልቸው ቢወተውቱም  ምላሽ ማጣታቸውን ተናግረዋል።
በሰባተኛው የአርሶአደሮች እና ከፊል አርብቶ አደሮች ስብሰባ ላይ የተገኘው ዘጋቢያችን   ያነጋገራቸው አርሶ አዶሮች “ከአምስት አመታት በፊት በሁለተኛው እና በሶስተኛው የአርሶ አደሮች በዓል ላይ በክልሉ ካቢኔ ጎትጓችነት የኢንዱስትሪ አክሲዩን ባለቤት ትሆናላችሁ በሚል ጥሪታችንን አሟጠን፣  ከ70ሺ ብር ጀምሮ በየአመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ብናዋጣም እስካሁን ምንም ነገር ለማየት አልቻልም” ብለዋል።
ከስራ አሰፈፃሚው አቶ አለምነው መኮንን በተገኝ መረጃ መሰረት የአማራ ፐልፕ የወረቀት ፋብሪካን ለመገነባት ሙሉ በሙሉ ከተሸላሚ አርሶ አደሮቸ አክሲዩን እንዲዋጣ ተደርጎ  ከ 21 ሚልዩን ብር በላይ ተሰብስቧል። 

መንግስት በውጭ የሚኖረውን ዲያስፖራ ለመያዝ ይረዳኛል በሚል ከጀመራቸው የቤት ልማት ፕሮግራም ውስጥ 40 በ60 በሚባለው ፕሮግራም የሚገነቡ ቤቶች ከምርጫ 2007 በፊት ለተጠቃሚዎች ማስተላለፍ ሳይችል ቀረ፡፡

መጋቢት ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከሚቀጥለው ሳምንት ከመጋቢት 10 እስከ 13 ድረስ ባሉት ቀናት የአዲስአበባ አስተዳደር 20 በ80 ተብሎ
የሚታወቀውን የኮንዶሚኒየም 35 ሺ ቤቶች ዕጣ በማውጣት ለእድለኞች ለማስተላለፍ ያቀደ ሲሆን በዚህ የዕጣ አወጣጥ ፕሮግራም ላይ 40 በ 60 የሚባለውና አብዛኛው ዲያስፖራ ተመዝግቦበታል የተባለው ዕጣ እንደማይወጣ ታውቆአል፡፡
የአዲስአበባ ከተማ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ሰሞኑን በተካሄደው የአስተዳደሩ ም/ቤት ጉባኤ ላይ ባቀረቡት ሪፖርት እንደጠቆሙት 1 ሺ 200 ያህል 40 በ 60 የተገነቡ ቤቶች ግንባታቸው ባለመጠናቀቁ በመጪው ሰኔ ወር ለማስተላለፍ ዕቅድ ተይዞአል፡፡
ለዚህ ለ40 በ 60ፕሮግራም  የተመዘገበው 164 ሺ 779 ሕዝብ ሲሆን ለአንድ መኝታ ቤት በየወሩ 1 ሺ 33 ብር፣
ለሁለት መኝታ ቤት በየወሩ 1 ሺ 575 ብር፣ ለሶስት መኝታ ቤት በየወሩ 2 ሺ 453 ብር እየቆጠበ ይገኛል፡፡ ይህ የቤት ልማት ፕሮግራም ከሌላው ለየት የሚያደርገው መንግስት ምንም ዓይነት ድጎማ የማያደርግበትና ዕድለኞች የቤቱን ሙሉ ወጪ ከፍለው እንዲወስዱ የታሰበ መሆኑ ነው፡፡
በዚሁ መሰረት 40 በመቶ ባለዕድለኛው ሲከፍል 60 በመቶውን ከባንክ በሚገኝ ብድር ባለቤት ለማድረግ ታስቦ የተጀመረ ቢሆንም፣ በኃላ ላይ የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ መቶ በመቶ ቅድሚያ ለከፈለ ቅድሚያ ያገኛል የሚል በአንድ ወቅት መግለጫ መስጠታቸው ብዙዎችንተስፋ አስቆርጦአል፡፡
የአስተዳደሩ ምንጮች እንደሚናገሩት ይህም ሆኖ በርካታ ሰዎች መቶ በመቶ በመክፈላቸውና ቁጥራቸውም ከሚገነቡት ቤቶች በላይ በመሆኑ በዕጣ መለየት የግድ ሆኖአል፡፡
ምንጮቹ አያይዘውም የአስተዳደሩ ጥቂት ሃላፊዎች 40 በ60 ቤቶች መቶ በመቶ ቅድሚያ ለከፈሉ ቅድሚያ ይሰጥ የሚለው ከፕሮግራሙ ዓላማና ለሕዝብ ከተገባው ቃል ተቃራኒ በመሆኑ መተግበር የለበትም የሚል አቋም እንዳላቸው ታውቋል፡፡
በመሃል ከተማ በሰንጋ ተራና ክራውን ሆቴል አካባቢ  ጂ 12 እና ጂ 9 በሚል  የተገነቡት እነዚሁ ቤቶች ከተመዝጋቢው ቁጥር አንጻር ሲታይ  እጅግ አነስተኛና እዚህ ግባ የማይባል መሆኑን የጠቀሱት የአስተዳደሩ ምንጮች፣  የዘንድሮውን አፈጻጸም መነሻ በማድረግ በዓመት 1 ሺ 200 ቤቶች ይገነባሉ ቢባልም፣  164ሺ ቤት ለመገንባት ስንት ኣመት ሊፈጅ እንደሚችል ሲታሰብ ሥራው በመንግስት አቅም ብቻ ሊከናወን እንደማይችል በቂ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
በቀጣይ ሳምንት  እጣ ከሚወጣባቸው ቤቶች ውስጥ  1 ሺህ ቤቶች የ10 በ90 ማለትም ስቱዲዮ ክፍል ያላቸው ሲሆኑ፥ 34 ሺዎቹ ደግሞ የ20 በ 80 ወይንም ኮንዶሚኒየም የሚባሉት የጋራ መኖሪያ ቤቶች ናቸው።
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ በየካ አባዶ፣ ቦሌ ለሚ፣ ቦሌ ቡልቡላ እና ቱሉ ዲምቱ ሳይቶች እንደሚገኙ ታውቆአል፡፡

የግዲቾ ብሄረሰብ አባላት ያነሱትን ተቃውሞ ተከትሎ ፖሊሶች አንድ ሰው ገድለው 8 አቆሰሉ

መጋቢት ፬(አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግዲቾ ብሄረሰብ አባላት ተቃውሞውን ያስነሱት መሬታቸው ለትምባሆ ተክል እርሻ ለአንድ ባለሀብት መሰጠቱን ተከትሎ ነው።
በደቡብ ክልል በጋሞጎፋ ዞን በምእራብ አባያ ወረዳ የሚኖሩት ቁጥራቸው እስከ 5 ሺ የሚደርሱ የብሄረሰቡ አባላት፣ ቀደም ብሎ በአባያ ሃይቅ መካከል በሚገኘው ደሴት ይኖሩ ነበር። ደሴቱ በሃይቁ ሙሉ በሙሉ መሸፈኑን ተከትሎ የብሄረሰቡ አባላት ሃንቲ ወደ ሚባል አጎራባች ቀበሌ በመሄድ ኑሮአቸውን ሲገፉ ቆይተዋል።
ይሁን  እንጅ የዞኑ ምክር ቤት የእርሻ መሬታቸውን ለ4 ኢንቨስተሮች በመስጠቱ፣ ነዋሪዎቹ በእርሻ መሬት እጦት ሲሰቃዩ ቆይተዋል። ባለፉት ጥቂት ወራት ደግሞ የብሄረሰቡን አባላት ሙሉ በሙሉ በሚያፈናቅልና መድረሻ በሚያሳጣ ሁኔታ ፣ መሬታቸው ለአንድ ትምባሆ አምራች ኢንቨስተር ተሰጥቷል።
ነዋሪዎቹ  በተወካይ ሽማግሌዎች አማካኝነት አቤቱታቸውን ለዞኑና ለክልል ምክር ቤት አባላት ሲያቀርቡ ቢቆዩም፣ በየደረጃው ካሉ ባለስልጣናት ያገኙት መልስ ግን ስድብ ብቻ ነው።
ባለፈው ማክሰኞ አዲሱ ባለሃብት ወደ አካባቢው በመሄድ ደኖችን  መመንጠር ሲጀምር በአካባቢው የነበሩት ሴቶችና ህጻናት በመጮህ ተቃውመዋል። የአካባቢው ፖሊሶች ፈጥነው በመድረስ በጩኸት ሲቃወሙ ከነበሩት መካከል አንዷን አሮጊት ክፉኛ መደብደባቸውን፣ ጨኸቱን ሰምተው የተሰባሰቡት ወንዶችም ተቃውሞአቸውን መግለጻቸውን የአይን እማኞች ገልጸዋል።
ፖሊሶች ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ያገኙትን ሁሉ ከመደብደብ አልፈው ጥይቶችን በመተኮስ አንዱን የብሄረሰቡ አባል በ4 ጥይቶች አናቱን መትተው ሲበታትኑት፣ 8ቱን ደግሞ ክፉኛ አቁሰለዋቸዋል። አንደኛው ሰው አንጀቱ አካባቢ ተመትቶ የህክምና እርዳታ እያገኘ ቢሆንም፣ ላይተርፍ ይችላል ተብሎአል። ሌሎች ደግሞ እጅና እግራቸው መሰባበሩን የአይን እማኖች ለኢሳት ተናግረዋል።  
“በጣም የሚያሳዝነው” ይላሉ ነዋሪዎች፣ “ሟቹ ለ6 ሰአታት ያክል መንገድ ላይ ወድቆ አስከሬኑ እንዳይነሳ መደረጉ ነው”።
የብሄረሰቡ አባላት በከፍተኛ ድህነት ውስጥ የሚገኙ ሲሆን፣ መሬታቸው በጉልበት ለባላሀብቱ ከተሰጠ፣ ወደ ከተሞች ተሰደው የጎዳና ተዳዳሪ ሊሆኑ እንደሚችሉ ይናገራሉ።
በጉዳዩ ዙሪያ የጋሞጎፋ ዞን ፖሊስ ጽ/ቤትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል።

Thursday, March 12, 2015

በሲዳማ ዞን የአለታ ጩኮ ወረዳ ህዝብ በውሃ እና መብራት ማጣት እየተሰቃየ ነው

መጋቢት ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በወረዳው ውሃ ከ15 ቀን በላይ በመጥፋቱ ከጉረቤት ቀበሌያት እየተቀዳ የሚመጣው ንፅህናው ያልተጠበቀ አንድ ጀሪካን ውሃ እስከ 10 ብር እየተሸጠ ሲሆን ፣  ይህንኑ ውሃ በአህያ ጋሪ ከተማ ውስጥ ለመግዛት ነዋሪዎች ቀድመው ለመክፈል ይገደዳሉ ።
አንዲት የጪኮ01 ቀበሌ ነዋሪ የሆነችና በሰው ቤት የቀን ስራ ሰርታ የምትተዳደር ሴት  ” እቤቴ የአንድ አመት ልጅ አለኝ ልጄ በውሃ ጥም እየሞተ ነው ይኸው አንድ የታሸገ ውሃ በእጅዋ ይዛ እያሳየች ይህንን ለልጄ ስል በ15 ብር ገዛሁ ግን አቅሜ እንኳን ለታሸገ ውሃ ለዳቦም አልበቃ” ብላለች ።
ሌላውም አርሶ አደር ልጆቼን ከትምህርት ቤት አስቀርቻለሁ ምክንያቱም ውሃ በሌለበት አምኜ ከተማ ልጆቼን አልክም ብለዋል ። በአንዳንድ የከተማው ነዋሪዎች ቤት ውሃ ለሊት ለሊት የሚመጣ ሲሆን ስለዚሁ ጉዳይ የተጠየቁት የውሃ ጵ/ቤት ሃላፊ አቶ መኩሪያ፣ ችግሩ የተከሰተው ዋናው የውሃ ታንከር የሚያንቀሳቅሰው የኤሌክትሪክ መስመር በመበላሸቱ ምንም ማድረግ አልችልም በማለት ድፍን ያለ ምላሽ ሰጥተዋል ።
የወረዳው አስተዳደር ጉዳዮን ለመፍታት ያደረገው ሙከራ የለም የሚሉት ነዋሪዎች ለራሱ ቢሮ ጄኔሬተር በመግዛት እና የታሸገ ውሃ ለሃላፊዎች በማቅረብ የህዝቡን ችግር ረስቶታል ሲሉ መናገራቸውን የአካበባው ወኪላችን ገልጿል

አቶ በረከት ስምኦን ራሳቸውን ከምርጫ ክርክር አገለሉ

መጋቢት ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአለማቀፍ ታዛቢዎችና በኢትዮጵያውያን በቂ ትኩረት ያልተሰጠውን የግንቦት 16 ቀን 2007 ምርጫ ክርክር የሚሳተፉለትን መሪዎች ሲያፈላል የነበረው ኢህአዴግ፣ ለመጀመሪያው ዙር የክርክር መድረክ የሚሆኑትን ሰዎች ሲመርጥ፣ አቶ በረከት ራሳቸውን አግልለዋል።
ኢህአዴግ 23 አመራሮችን ለክርክር በእቅድ የያዘ ቢሆንም፣ ከእነዚህ ወስጥ በመጀመሪያው ዙር መጣሪያውን ያለፉት አቶ  ሬዲዋን ሁሴን  እና አቶ ደሰታ አስፋው ብቻ ናቸው። 21ዱ አመራሮች ቀጥተኛ ተፎካካሪ መሆን አይችሉም ተብለዋል።
በሁለተኛው ዙር ማጣራት አቶ አባይ ፅሃየ ፣ካሳ ተክለብርሃን ፤ ተፈራ ደርበው ፤ሽመልስ ከማል እንዲያልፉ ተደርጓል። ኢህአዴግ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ማህደር ሲያጠና ከርሞ ዛሬ በዝግ ለተከራካሪ አመራሮች ገለጻ እያደረገ ነው።
በመጀመሪያው ዙር በእጩነት ቀርበው አይመጥኑም፣ ኢህአዴግን ያዋርዱታል ከተባሉት ውስጥ አባ ዱላ ገመዳ፣ አስቴር ማሞ፣ ዘነቡ ታደሰ፣ ሙፈሪያት ከማል፣ ከበደ ጫኔ፣ ወልዱ ይምሰል፣አህመድ አብተው፣ ተመስገን ጥላሁን፣ አሊ ሲራጅ፣ ታደሰ ሃይሌ፣ ፍሬህይወት አያሌውና ብስራት ጋሻው ይገኙበታል።
በረከት ስምኦን በክርክር መድረኮች ላይ እንዲገኙ ቢጠየቁም አልፈልግም በሚል ራሳቸውን አግልለዋል። ራሳቸውን ለማግለላቸው የሰጡት ምክንያት የለም።  ከመጋቢት 04 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ በሚካሄደው የፓርቲዎች ክርክር ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግን ጨምሮ በአንድ የክርክር መድረክ ላይ አምስት ፓርቲዎች የሚሳተፉ  ሲሆን በአጠቃላይ ዘጠኝ መድረኮች ይካሄዳሉ።
ፓርቲዎቹ በተመረጡት አጀንዳዎች ላይ ያላቸውን አቋም በሚገባ ለማንጸባረቅ በአንድ የክርክር መድረክ የሚሳተፉት ፓርቲዎች ብዛት አምስት እንዲሆን ተደርጓል። በክርክሩ ላይ ተቃዋሚዎች እያንዳንዳቸው አንድ ተከራካሪ  እና  አንድ አማካሪ እንዲሁም ገዢው ኢህአዴግ ሁለት ተከራካሪና አንድ አማካሪ  በመያዝ ይከራከራሉ። የዘንድሮውን ምርጫ የአውሮፓ ህብረት አይታዘበውም። ህብረቱ በምርጫው መሳተፍ ዋጋ የለውም በሚል ምክንያት መሆኑን በቅርቡ በህብረቱ ውስጥ በተዘጋጀ አንድ ዝግጅት ላይ ተገልጿል።

እንግሊዝ ከሰብአዊ መብቶች ጋር በተያያዘ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን እርዳታ ማቋረጡዋን አስታወቀች

መጋቢት ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ብሉምበርግ የእንግሊዝ ባለስልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው እንግሊዝ በኢትዮጵያ ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለመደጎም ትሰጥ የነበረውን እርዳታ ያቋረጠችው፣ መንግስት መጪውን ምርጫ ተከትሎ ጋዜጠኞችንና የተቃዋሚ ፓርቲ አባሎችን ማሰሩንና መዋካቡን በመቀጠሉ ነው።
የእንግሊዝ አለማቀፍ የልማት ተራድኦ ጸሃፊ ጀስቲን ግሪኒንግ ፣ እንግሊዝ አጠቃላይ የሆነ የኢኮኖሚ ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑዋን ተከትሎ፣ ቀድም ብሎ ይሰጥ የነበረው የማህበራዊ አግልግሎት ድጋፍ እንደተቋረጠ ለእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ቀርበው አስረድተዋል።
ባለስልጣኑ በኢትዮጵያ የሚፈጸመው የሰብአዊ ና የፖለቲካ ነጻነቶች ገፈፋ አሳሳቢ መሆኑ እርዳታው እንዲቋረጥ አድርጎታል። በተለይም ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ ነጻ ምርጫ የማካሄድና የጸጥታ ሃይሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ነገር አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ለተወሰደው እርምጃ ምክንያት መሆኑን ባለስልጣኑ ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።
የእንግሊዝ ተራድኦ ድርጅት በዚህ አመት 368 ሚሊዮን ፓውንድ ወይም በኢትዮጵያ ብር 11 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመስጠት አቅዳ ነበር፧ ባለፉት አምስት አመታት ከ700 ሚሊዮን ፓውንድ ያላነሰ ገንዘብ ደግፋለች

እንግሊዝ ከሰብአዊ መብቶች ጋር በተያያዘ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን እርዳታ ማቋረጡዋን አስታወቀች

መጋቢት ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ብሉምበርግ የእንግሊዝ ባለስልጣናትን ጠቅሶ እንደዘገበው እንግሊዝ በኢትዮጵያ ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለመደጎም ትሰጥ የነበረውን እርዳታ ያቋረጠችው፣ መንግስት መጪውን ምርጫ ተከትሎ ጋዜጠኞችንና የተቃዋሚ ፓርቲ አባሎችን ማሰሩንና መዋካቡን በመቀጠሉ ነው።
የእንግሊዝ አለማቀፍ የልማት ተራድኦ ጸሃፊ ጀስቲን ግሪኒንግ ፣ እንግሊዝ አጠቃላይ የሆነ የኢኮኖሚ ድጋፍ ለማድረግ መወሰኑዋን ተከትሎ፣ ቀድም ብሎ ይሰጥ የነበረው የማህበራዊ አግልግሎት ድጋፍ እንደተቋረጠ ለእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ቀርበው አስረድተዋል።
ባለስልጣኑ በኢትዮጵያ የሚፈጸመው የሰብአዊ ና የፖለቲካ ነጻነቶች ገፈፋ አሳሳቢ መሆኑ እርዳታው እንዲቋረጥ አድርጎታል። በተለይም ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ ነጻ ምርጫ የማካሄድና የጸጥታ ሃይሎችን ተጠያቂ የማድረጉ ነገር አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ ለተወሰደው እርምጃ ምክንያት መሆኑን ባለስልጣኑ ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።
የእንግሊዝ ተራድኦ ድርጅት በዚህ አመት 368 ሚሊዮን ፓውንድ ወይም በኢትዮጵያ ብር 11 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመስጠት አቅዳ ነበር፧ ባለፉት አምስት አመታት ከ700 ሚሊዮን ፓውንድ ያላነሰ ገንዘብ ደግፋለች

የአዲስ አበባ ከንቲባ የከተማዋን የጸጥታ ጉዳይ ለኦሮምያ ምክር ቤትም ሪፖርት እንዲያቀርቡ ታዘዙ

መጋቢት ፫(ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዲስ አበባንና የኦሮምያን የጸጥታ ሁኔታ ለማስተሳሰር፣ የኦሮምያን ልዩ ሃይልና የፌደራል ፖሊሶችን በጋራ በአዲስ አበባ ለመጠቀም ሲባል፣ መስተዳድሩ የጸጥታ ጉዳዮችን ለጨፌ ኦሮምያም ጭምር ሪፖርት እንዲያደርግ ታዟል።
የእቅዱ ዋና ነዳፊ የሆኑት የጠ/ሚኒስትሩ አማካሪ አባይ ጸሃየ፣ ጸጥታን በተመለከተ የኦሮምያ ምክር ቤት ሪፖርት እንዲቀርብለት፣ የልማት ጉዳዮችን በተለይ መሬትን በተመለከተ ደግሞ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ሪፖርት እንዲቀርብለት አዘዋል። ምርጫው ተጠናቆ አዲስ ምክር ቤት እስከሚመሰረት ድረስ በዚህ መንገድ እንዲቀጥል  አባይ ጸሃየ ቢያዝዙም፣ ከንቲባ ድሪባ ኩማ ሳይቀበሉት ቀርተዋል። ትእዛዙ ወደ ምክትል ከንቲባው አባተ ስጦታው እንዲወርድ ቢደረገም፣ አቶ አባተ ኦሮምኛ አይችሉም በሚል አቶ ድሪባ በግድ እንዲቀበሉት ተደርጓል።
ከንቲባ ድሪባ ጨፌ ኦሮምያ ተገኝተው ሪፖርት የቃረቡ ቢሆንም፣ ከምክር ቤት አባላት የተነሱትን ጥያቄዎች መመለስ ሳይችሉ ቀርተዋል። ከንቲባ ድሪባ ” የአዲስ አበባ የጸጥታ ጉዳይ ለምርጫው ሲባል በኦሮምያ ምክር ቤት እንዲደመጥ ተወስኗል” ብለዋል።
በአዲሱ አሰራር የኦሮምያ ክልል ምን እንደሚያገኙ የጠየቁት የምክር ቤት አባላት በቂ ምላሽ አላገኙም። ይሁን እንጅ አሁንም መሬት ለማስፋት፣ የኦሮምያና የአዲስ አበባ ክልሎችን በማጣረስና ውሳኔዎችን በመደራራብ ችግር ለመፍጠር ታስቦ የተካሄ እንዳይሆን ፣ አካሄዱም ኢህአዴግን ለከፋ ችግር ሊዳርገው እንደሚችል ተናግረዋል።

Wednesday, March 11, 2015

የኢትዮጰያ መንግስት  በተያዘው ዓመት 3 ሚሊዮን ለሚጠጉ ሰዎች እርዳታ  እንደሚያስፈልገው ማሳወቁን ተመድ ገለጸ።

መጋቢት ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ተመድ የመንግስትን ሪፖርት ዋቢ አድርጎ ባወጣው መግለጫ ዘንድሮ  በኢትዮጰያ 2.9 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ብሏል።
ከተረጅዎቹ መካከል 38 በመቶው  ከኦሮሚያ፣ 31 ከመቶው ደግሞ ከሶማሌ፣ 12 በመቶው ከትግራይ እና 6 በመቶው ካማራ ክልሎች መሆናቸውን ሪፖርቱ ያመለክታል። ለተረጅዎቹ ድጋፍ ለማድረግ  386 ሚሊዮን ዶላር  እንደሚያስፈልግ ያመለከተው ተመድ፤ ይሁንና  የረድኤት ድርጅቶች የፈንድ እጥረት እንዳለባቸው በመግለጽ ላይ መሆናቸውን ጠቁሟል።
በተያያዘ ዜና የጋምቤላ ክልል ባለስልጣናት  ከጋምቤላ ከተማ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ  በሚገኝ ቦታ <<ጄዊ>> የተሰኘ  አዲስ ካምፕ ማዘጋጀታቸውን የጠቀሰው ተመድ፤ 50 ሺህ ሰዎችን የመያዝ አቅም ይኖረዋል የተባለው ይህ ካምፕ  ስደተኞች ወደ ማምረት ስራ እንዲገቡ የሚያመች እንደሆነ  ቅኝት ለማድረግ ወደ ስፍራው ተንቀሳቅሰው የነበሩ የስደተኞች ጉዳይ  ከፍተኛ ኮሚሺነር ቡድን  አባላትን በመጥቀስ ገልጿል።
አዲሱን ካምፕ ለማሳደግና ለማስፋፋት የኮሚሺኑ ተጨማሪ 16.5 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው በሪፖርቱ ተመልክቷል። ተመድ የመንግስትን ሪፖርት ተንተርሶ  ዘንድሮ  በኢትዮጰያ 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ሰዎች   አስቸኴይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ያወጣውን ሪፖርት  እንደማይቀበሉት ኢሳት ያነጋገራቸው  አንድ የረድኤት ድርጅት ሰራተኛ ተናግረዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የትውልድ መንደር  ነዋሪዎች በውሀ፣ በመብራትና በስልክ ችግር ክፉኛ እያማረሩ ነው።

መጋቢት ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ነዋሪዎቹ  ምሬታቸውን ለኢሳት ሲግልጹ፦” አቶ ሀይለማርያምን  ከልባችን አውጥተን ከጣልነው ቆይተናል” ብለዋል።
በደቡብ ክልል በወላይታ ዞን   የጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ የትውልድ ቦታ የሆነችው  የአረካ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት  በጠቅላላ የወላይታ ዞን  ነዋሪዎች በውሀ፣በመብራትና በስልክ ችግር  መማረር ከጀመሩ ረዥም ጊዜያት ሆኗቸዋል።
በተለይ ካለፉት ሁለት ወራት  ወዲህ የአቶ ሀይለማርያም የትውልድ መንደር በሆነችው  በአረካ አገልግሎቱ ጠቅላላ የቆመበት ደረጃ ላይ መድረሱን የተናገሩት ነዋሪዎቹ፤ በዚህም ሳቢያ  አንድ ጀሪካን ውሀ እስከ 15 ብር ድረስ እየተሸጠ መሆኑን  ጠቁመዋል።
የወረዳው ብቻ ሳይሆን  በአጠቃላይ የዞኑ ህዝብ  ጠቅላይ ሚኒስትሩን  እየረገመና እያወገዘ እንደሚገኝ የተናገሩት ነዋሪዎቹ፤ “እንዲህ የቀለዱብን ብንመርጣቸውም፣ባንመርጣቸውም ኮሮጆ የመገልበጥ  ልምዱን ስለተካኑበት ነው” ብለዋል።
“ህዝቡ እጅግ ተማርሯል፤ ወደ ጨለማ ዘመን እየተመለስን ነው፣ ምን እናድርግ? ብሶታችንን ለማን እንናገር?” ያሉት ነዋሪዎቹ፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ተስፋ አድርገን የነበረ ቢሆንም፤ ገዥው ፓርቲ በሆነ ባልሆነው ሰበብ እየፈለገ እያጠፋቸው ነው።”ብለዋል።
ችግሮቹን አስመልክተው ለሚመለከታቸው አካላት በተደጋጋሚ አቤቱታ ቢያቀርቡም ምንም ዓይነት ተግባራዊ ምላሽ ሊያገኙ አለመቻላቸውን የተናገሩት  የአርኪያ ነዋሪዎች፤ “ወዴት እንሂድ?”ሲሉ  ምሬታቸውን ገልጸዋል

በኢትዮጰያ ህዝባዊ ስብሰባዎችና ሰልፎች  ቢታገዱም ህዝቡ በስርዓቱ ላይ ያለውን ተቃውሞ በተለያዩ መንገዶች መግለጹን ቀጥሏል።

መጋቢት ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በተለይ በአዲስ አበባ በተለያዩ ስፍራዎች  የሚገኙ ግድግዳዎችና የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች በየእለቱ “ጭቆና በቃን! ነጸነትና ፍትህ እንፈልጋለን!  ለነጸነት ትግል ተነስ!” በሚሉ መፈክሮች አሸብርቀው መታየታቸው የተለመደ ሆኗል።
በቅርቡ ደግሞ  እነኚሁ  የፍትህና  የነጻነት ጥያቄዎች በመገበያያ የብር ኖቶች ላይ ሳይቀር በስፋት  እየተስተዋሉ መሆናቸው  የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። ሂደቱ በዚህ ከቀጠሉ  የብር ኖቶች በሙሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ በመፈክር ጽሁፎች መጥለቅለቃቸው እንደማይቀርም መረጃውን ያደረሱን አካላት  ገልጸዋል።
ከዚህም ባሻገር የአንዳንድ ነጋዴዎች ምርቶች ሳይቀር በታሰሩ የነጻነት ታጋዮች ስም ተሰይመው መታየታቸውን የግለጹት ምንጮች፤ይሁንና  ይህ የሆነው በስም መገጣጠም ይሁን አለያም አምራቾቹ ሆነ ብለው በነጻነት ታጋዮቹ ስም ሰይመው በእርግጥኝነት እንዳላወቁ አልሸሸጉም።
ከነዚህ ምርቶች መካከል በየሱቆች በስፋት እየተሰራጬ የሚገኘው “ርእዮት ሳሙና” አንዱ ነው።
ጉዳዩን አስመልክቶ  የ ርእዮት እህት እስከዳር ዓለሙ በፌስ ቡክ ገጿ ባሰፈረችው አስተያየት ፦”የእኛሰፈርሱቆችይህንንምርትበየመደርደሪያቸዉሞልተዉትሳይይህችልጅበጽሑፏለማፅዳትየሞከረችውአልበቃብሏትበፈሳሽሳሙናመልክመጣችእንዴ?ብዬአሰብኩ ” ብላለች።
ባለፉት ወራት በቦሌ አካባቢ የሚገኙ ግድግዳዎችና አጥሮች ፦”መሪዎቻችን  ይፈቱ!  ፍትህ ለኮሚቴዎቻቸን! ጭቆናው ይብቃ!”በሚሉና በሌሎች መሰል መፈክሮች  ተሞልተው መታየታቸው ይታወሳል።

የሱማሌ ክልል ፕሬዚዳንት በዋሽንግተን ዲሲ  ለደረሰባቸው የኢትዮጰያውያን ተቃውሞ የብልግና ምላሽ ሰጡ።

መጋቢት ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሱማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር በዋሽንግተን ዲሲ ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጠማቸው።
ፕሬዚዳንቱ በተገኙበት ሆቴል የተገኙ ኢትዮጰያውያን ፦” ሰውዬው እጃቸው በደም የተጨማለቀ፣ የሱማሌ ክልል ወጣቶችን በመግደል በዘር ማጥፋት ክስ የተመሰረተባቸውና  እና ለዚህም  በዓለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ሊጠየቁ የሚገባ  ወንጀለኛ መሆናቸውን በማውሳት ከፍ ያለ ተቃውሞ አሰምተዋል።
በደረሰባቸው ድንገተኛ ተቃውሞ  የተበሳጩ የመሰሉት የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሀመድ  በተደጋጋሚ ጸያፍ ቃል ሲናገሩ ተደምጠዋል። ስለ ሁኔታው መረጃ ደርሰሠቸው በስፍራው የደረሱ የሴኩሪቲ ሰራተኞችም   ተቃውሞውን አብረደውታል።

Tuesday, March 10, 2015

ጄ/ል ሳሞራ የኑስ በአየር ሃይል አባላት ላይ እየዛቱ መሆናቸው ተሰማ

መጋቢት ፩(አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አብራሪዎች ባለፉት 6 ወራት ከድሬዳዋ አየር ሃይል ግቢ ጠፍተው ተቃዋሚዎችን መቀላቀላቸውንና መሰደዳቸውን ተከትሎ ኢታማዦር ሹሙ ሳሞራ የኑስ በቀሪዎቹ ላይ የዛቻና የማስፈራሪያ ንግግሮችን በማድረግ ላይ መሆናቸው ተሰምቷል ።
የአየር ሃይል ምንጮች እንደተናገሩት፦ጀነራሉ <<ከጠፉት የአየር ሃይል አባላት ጋር ግንኙነት ነበራቸው>>ያሏቸውንና  <<ሊጠፉ ሲሉ ተያዙ የተባሉ ሌሎች የአየር ሃይል አባላትን>>  ለቀሪዎቹ አባላት ሲያሳዩ ሰንብተዋል። ኢታማዦር ሹሙ  ሰሞኑንም እነኚህኑ <<ከተቃዋሚዎች ጋር ግንኙነት አላቸው>> ያሏቸውን አባላት፦ ” የውስጥ ተቃዋሚዎች” ተያዙ በማለት በተለያዩ የአየር ሃይል ግቢዎች እያዞሩ በማሳየት ሌሎችን የአየር ሀይሉን አባላት ለማስፈራራት ሙከራ በማድረግ ላይ መጠመዳቸው ታውቋል።
እንደ ምንጮች ገለጻ፦ <<ሊጠፉ ሲሉ ተያዙ>> የተባሉ የተለያዩ የአየር ሃይል አባላት  የእስረኛ ህጋዊ መብታቸው ተገፎ በሌሎች የአየር ሃይል አባላት ፊት ቀርበው እንዲሸማቀቁና ክብራቸው እንዲነካ መደረጉ፤ ብዙ የአየር ሃይል አባላትን አስቆጥቷል።
እነዚሁ የአየር ሀይል ምንጮች፤አብራሪዎቹ እውነት ተቃዋሚዎች ናቸው ቢባል እንኳ ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው፣ ታስረው ሰራዊቱ ፊት እንዲቀርቡ መደረጉ የአገዛዙን ባህሪ ያሳየነ ነው በማለት  ለኢሳት ገልጸዋል።
የአየር ሃይል አባላት አምነውበት ማገልገል ሲገባቸው በማስፈራራት በሰራዊቱ ውስጥ እንዲቆዩ ለማድረግ የሚደረገው መኩራ ቁጣንና ቅሬታን ከማባባስ ውጭ የሚፈይደው ነገር እንደሌለም እነዚሁ  የአየር ሀይል አባላት ተናግረዋል።
ጄ/ል ሳሞራ  ከዚያም አልፈው ፦<<ኢሳት ኤርትራ ውስጥ ቃለ-መጠይቅ ያደረገላቸውን አብራሪዎችንና ቴክኒሻኖችን ይዘን እናመጣቸዋለን>> እያሉ ሲዝቱ እንደነበር፤ በግምገማ ተወጥረው የሰነበቱት የአየር ሃይል አባላት ተናግረዋል።
በአየር ሃይል አባላትና- በሰራዊቱ ከፍተኛ አዛዦች መካከል መተማመን መጥፋቱን የሚናገሩት እነኚሁ የአየር ሀይል ባልደረቦች፣ በዚህም ምክንያት ጄ/ል ሳሞራና ሌሎች አዛዦች ግራ እንደተጋቡ አክለዋል።
በመጀመሪያ <<ምን እናድርግላችሁ?>> በሚል የማባበል ቃል  መቀራረብ ለመፍጠር ቢሞክሩም  ሰራዊቱ የሚያነሳው የመብት ጥያቄ በቀላሉ የሚመለስ ሆኖ ባለመገኘቱ ወደ ማስፈራራት መገባቱን የአየር ሃይል አባላቱ ይናገራሉ።

2 ዳንኤል ሺበሺ
3 የሽዋስ ዛሬ በዋለው ችሎት የፍርድ በቱን ችሎት በመድፈር ምክንያት ተብሎ የ7 ወር የእስር ፍርድ የተፈረደባቸው ሲሆን አብርሃ ደስታ ወደ ማዕከላዊ እንዲመለስም ታዞዋል።
በተያያዘ ዜና እነ ሃብታሙ አያለው ደግሞ ለመጋቢት 3 ተቀጥረዋል።
Unlike ·  ·