Tuesday, June 2, 2015

ከኬንያ ተጠልፈው የነበሩት ሁለቱ የኦብነግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ ናይሮቢ ተመለሱ

ግንቦት ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአንድ ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች ከኬንያ ተጠልፈው ወደ ኢትዮጵያ ተወስደው የነበሩት አቶ ሱሉብ አብዲ አህመድና አቶ አሊ አህመድ ሁሴን ትናንት ምሽት
ኬንያ ናይኖቢ መግባታቸውን ለኢሳት ደረሰው መረጃ አመልክቷል።
ሁለቱ ከፍተኛ አመራሮች በምን ሁኔታ ወደ ናይኖቢ እንደተመለሱ የታወቀ ነገር የለም። የድርጅቱ የውጭ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አብድረህማን ሼህ ማህዲ የመሪዎቹን ወደ ናይሮቢ መመለስ አረጋግጠው፣ በምን ሁኔታ እንደተመለሱ ግን ድርጅቱ
መግለጫ እንደሚሰጥ ለኢሳት ተናግረዋል።
በኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅትና በኢህአዴግ መካከል ድርድር እየተካሄደ ነው ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፣ ከዚህ በፊት አንዳንድ የድርድር ሙከራዎች ቢደረጉም፣ በአሁኑ ሰአት የሚደረግ ምንም አይነት ድርድር የለም ብለዋል።
የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት አማካሪ አብዲኑር አብዱላሂ ፋራህ የኦብነግ መሪዎቹ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል እጃቸውን ለመንግስት መስጠታቸውን ገልጸው ነበር።
በሌላ ዜና ደግሞ ባለፉት 5 ቀናት በኢህአዴግ ወታደሮች የሚደገፉት የሶማሊ ክልል ልዩ ሚሊሺያ አባላት በኢትዮ- ሶማሊ ድንበር አካባቢ በሚኖሩ አርብቶ አደሮች ላይ በወሰዱት እርምጃ የሟችና ቁስለኞች ቁጥር ማሻቀቡን የደረሰን መረጃ
ያመለክታል።
አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ 35 ሲቪሎች መገደላቸውን ቢዘግብም፣ የኢሳት ምንጮች ግን የሟቾቹን ቁጥር ከ70 በላይ ያደርሱታል። በርካታ ቁስለኞች ህክምና እንዳያገኙ በኢህአዴግ ወታደሮች በመከልከላቸው ለከፋ ችግር መጋለጣቸውንም
የደረሰን ዜና ያመለክታል። ግጭቱ መዋጮ ከመሰብሰብ ጋር ተያይዞ መነሳቱን ኦብነግ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
በሌላ በኩል ደግሞ ከቀናት የተኩስ ልውውጥ በሁዋላ በደቡብ ክልል በሃመር ወረዳ አንጻራዊ ሰላም መስፈኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።
በርካታ አርብቶ አደሮች በመከላከያ ሰራዊት አባላት መገደላቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ ካለፉት 3 ቀናት ጀምሮ የተኩስ ድምጽ አለመስማታቸውን ገልጸዋል። አርብቶአደሮቹ ትናንት ጥቃት እንደሚፈጽሙ ማስጠንቀቂያ ልከው የነበረ ቢሆንም፣
ዲመካ ከተማና አካባቢዋ ሌሊቱን በሰላም አሳልፈዋል። የመከላከያ ሰራዊት አባላትና ፖሊሶች በብዛት ተሰማርተው እንደሚገኙም ነዋሪዎች ይገልጻሉ።

Thursday, May 28, 2015

የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ለመሆን ሲወዳደሩ ከነበሩት እጩዎች መካከል የኢትዮጵያው የገንዘብ ሚኒስትር ሶፊያን አሕመድ ተሰናበቱ።

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እንደ አዲስ ስታንዳርድ ዘገባ እየተካሄደ ባለው ዓመታዊው የባንኩ የቦርድ ስብሰባ ላይ ነው ለፕሬዚዳንትነቱ ሲወዳደሩ ከነበሩት ስምንት ዕጩዎች መካከል የገንዘብ ሚኒስትሩ ሶፊያን አህመድ የሴራውሊዮኗን ሳሞራ ሚሸል ካማራን ተከትለው ሁለተኛው ተሰናባች ሆነዋል።
ቦርዱ እንደ አውሮፓያኑ አቆጣጠር ባለፈው ፌብሩዋሪ 11 ቀን አቢጃን በሚገኘው የባንኩ ዋና ጽህፈት ቤት ባደረገው ስብሰባ ባንኩን በፕሬዚዳንትነት ለመምራት ኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስትርን ጨምሮ ስምንት ስዎች በእጩነት መቅረባቸው ይታወቃል።
ይህም የሆነው አቶ ሶፊያንና ሌሎቹ ዕጩዎች ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር በሩዋንዳ-ኪጋሊ በተካሄደው የባንኩ ስብሰባ ላይ ፕሬዚዳንት ለመሆን እንደሚፈልጉ ፍንጪ በማሳየታቸው ነበር።
ላለፉት አስር አመታት ባንኩን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የቆዩት ዶናልድ ካቤሩካ በዚህ ዓመት መጨረሻ ሥልጣናቸውን ይለቃሉ።
ጋዜጣው እንደዘገበው የተለያዩ አገር መንግስታት በእጩነት የቀረቡት ዜጎቻቸው እንዲመረጡ ቅስቀሳ ቢያደርጉም ፣ የኢህአዴግ መንግስት ግን ለአቶ ሶፍያን ቅስቀሳ አላደረገም። መንግስት ለአቶ ሶፍያን ቅስቀሳ ለማድረግ ለምን እንዳልፈለገ የገለጸው
ነገር የለም። አቶ ሶፍያን ለአፍሪካ ህብረት መወደዳራቸው በመጪው ጊዜ በስልጣን ላይ እንደማይቆዩ አመላካች ሆኗል

በምርጫ ቦርድ ውጤት የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል

ግንቦት ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ የግንቦት15ቱን ምርጫ መቶ በመቶ ማሸነፉ ከተገለጸ በሁዋላ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ከሁለት ተከፍለዋል። ምንጮች እንደገለጹት በርካታ ፊደል ቀመስ አባሎቹ ኢህአዴግ አሸነፍኩ
ያለበትን የድምጽ ልዩነት አልተቀበሉትም። ውጤቱን የሚቃወሙ የግንባሩ አባላት ” ህዝቡ ከእንግዲህ በሰላም መንግስት እቀይራለሁ የሚለው እምነቱ ተሟጦ የሃይል አማራጭን ብቻ እንዲመለከት ከማድረጉም በላይ፣ የሃይል አማራጭን
የሚከተሉ ሃይሎች በህዝቡም ሆነ በአለማቀፉ ማህበረሰብም የተሻለ ተቀባይነት እንዲያገኙ ያደርጋቸዋል” በማለት ለድርጅቱ አስተያየታቸውን እየሰጡ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ተገኘ የተባለውን ውጤት ከመደገፍ አልፈው፣ ህዝቡ እንዴት ለተቃዋሚዎች ይህን ያክል ድምጽ ሊሰጥ ቻለ በማለት በቁጭት አስተያየት የሚሰጡ ደጋፊዎች መኖራቸውንም ምንጮች ገልጸዋል።
ኢህአዴግ እያሰባሰበ ባለው መረጃ ላይ እንደተገለጸው፣ አንዳንዶች ” ይህ ህዝብ ምን አይነት ልቡ የማይታወቅ ከሃዲ ህዝብ ነው! እንዴት ይሄን ሁሉ ልማት እያዬ ለተቃዋሚ ድምጹን ሊሰጥ ቻለ?” የሚል አስተያየት ሰንዝረዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ምርጫ ቦርድ ራሱ ባወጣው ሰሌዳ መሰረት የምርጫውን ውጤት መግለጽ የነበረበት ግንቦት21 ቢሆንም፣ የግንቦት20 በአልን ለማድመቅ እንዲረዳ በሚል ከእቅዱ በፊት እንዲገለጽ መደረጉን ምንጮችን ዋቢ በማድረግ
ዘጋቢያችን ገልጿል።
ኢህአዴግ በየክልሉ ከፍተኛ ወጪ የወጣበት የፌሽታ በዓላትን አዘጋጅቷል። ትናንት የገዢው ፓርቲ ደጋፊ አርቲስቶች ያዘጋጁት የኪነጥበብ ምሽት በብሔራዉ ቲያትር ተካሂዷል፡፡፡ በርካታ የፌዴራል የመንግስት መ/ቤቶች በተለያዩ ሆቴሎች
በዓሉን ለማክበር ጥሪ አስተላልፈዋል።
ምርጫ ቦርድ የኢህአዴግን አሸናፊነት ቢያውጅም መድረክ የተባለው የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ስብስብ የምርጫውን ውጤት አልተቀበለውም። ድርጅቱ ምርጫው አነስተኛ የሚባሉ መስፈርቶችን እንኳ ያላሟላ በማለት አጣጥሎታል። መድረክ
በአገሪቱ ውስጥ ያሉ ገለልተኛ የሚባሉ ሰዎች ተመርጠው መምርራ እንዲያካሂዱ ጠይቋል።
ሰማያዊ ፓርቲ ምርጫውን በተመለከተ ይህን ዜና እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ ያለው ነገር የለም። መንግስት የሰማያዊ ፓርቲ ደጋፊዎችን እያዋከበ በማሰር ላይ መሆኑ፣ ፓርቲውን አጣብቂኝ ውስጥ ሳይከተው አልቀረም። ሰማያዊ የምርጫውን
ውጤት ይቀበለዋል ተብሎ አይጠበቅም።
የአሜሪካ መንግስትና የአውሮፓ ህብረት ምርጫውን በተመለከተ በርካታ እጸጾችን አውጥተው ቢገልጹም፣ ከኢህአዴግ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንደማያቋርጡ አስታውቀዋል። የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ባወጣው መግለጫ ዲፕሎማቶች
በምርጫ ታዛቢነት እንዳይሰታፉ መከልከላቸው፣ ምርጫው አሳታፊ አለመሆኑንና የተለያዩ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች መታሰራቸውን በመግለጫቸው አመልክተዋል።
በምርጫው ሂደት ያጋጠሙ በርካታ አስገራሚ ክስተቶች ለኢሳት እየደረሱ ነው። ግንቦት12 ቀን 2007 ዓም በአዲስ አበባ ልዩ ቦታው ላንቻ ወይም ጠመንጃ ያዥ ነዋሪ የሆነ አንድ የ12 ዓመት ህፃን የኢህአዴግን የምርጫ መልዕክት ያየዘ
ፖስተር ከተለጠፈበት ግድግዳ ላይ ቀደሃል በሚል 6 ወር ተፈርዶበታል።
በአዲስ አበባ ችሎት በሚባል ቦታ አርብ ግንቦት 14 ቀን 2007 ዓ.ም ሁለት ማየት የተሳናቸው ወጣቶች ተይዘው ታስረዋል። ወጣቶቹ የተያዙት አንደኛው ሙሉ ሰማያዊ ልብስ ለብሶ በመውጣቱ በተፈጠረው አተካራ ነው። የአካባቢው
ሴት ካድሬ አንደኛውን ማየት የተሳነው ወጣት “ለምን ሰማያዊ ልብስ ለበስክ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ነሆይ?” በማለት ጥያቄ ስታቀርበለት፣ ጓደኛው “ምን አገባሽ ምንስ ብለብስ!” የሚል መልስ መስጠቱን ተከትሎ፣ ግለሰቧ በብስጪት
ለደህንነቶች ባስተላለፈችው ጥቆማ መሰረት ሁለቱም ወጣቶች በድንገት ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን እስከዛሬ ድረስ ታስረው ይገኛሉ።
መነን መሰናዶና 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም ፀሃይ ጮራ ት/ቤት ውስጥ የሚገኙ ቁጥራቸው 20 መምህራንና 30 ተማሪዎች የሰማያዊና የአንድነት ፓርቲ አባላት ናቸው በሚል ዝርዝራቸው ለጸጥታ አካላት ተልዕኮ በልዩ ሁኔታ ክትትል እንዲደረግባቸው ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከምርጫ በፊት ትዕዛዝ ተላልፎ እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

Thursday, May 14, 2015

በቴፒ 5 ሰዎች ተገደሉ

በጋምቤላና ደቡብ ክልል ድንበር አካባቢ የሪ በምትባል ቀበሌ 7 ሰዎች በተገደሉ ማግስት ሌሎች 5 ሰዎች ደግሞ በቴፒ ከተማ እንድሪስ ቀበሌ ውስጥ ከሌሊቱ 8 ሰአት ላይ በጥይት ተደብድበው መሞታቸውን የአካባቢው ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል።
የአካባቢው ሰዎች እንደሚሉት ከሟቾቹ መካከል አባትና ልጅ ይገኙበታል። ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ ገዳዮቹ ፖሊሶች ናቸው። ነዋሪዎች እንደሚሉት ሰዎቹ ይተገደሉት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ አማጽያንን ያስጠጋሉ፣ ይደግፋሉ ተብለው ነው። ኢሳት ለከተማው ፖሊስ በመደወል ለማጣራት ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካም።
ኢሳት ከሶስት ቀናት በፊት “ከመስከረም ወር ጀምሮ በቴፒና አካባቢዋ ያለው ግጭት ተባብሶ በመቀጠሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ስጋት ላይ መውደቃቸውንም፣ በእየለቱ በከተማዋ ውስጥ የጥይት ድምጽ እንደሚሰማና በርካታ ቁጥር ያላቸው የሸኮ መዠንገር ነዋሪዎች እየፈለሱ ወደ ቴፒ ከተማ በመግባት ላይ መሆናቸውን ” ዘግቦ ነበር።
ነዋሪዎች ጸጥታውን የሚያስከብርልን ሃይል አጥተናል በማለት በተደጋጋሚ አቤቱታ ያሰማሉ።

Monday, May 4, 2015

የኢህአዴግ ከፍተኛ ካድሬዎች በድርጅታቸው ግራ ተጋብተዋል

ሚያዝያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ የተገደሉትን ኢትዮጵያውያንን ለመዘከር የወጣው ህዝብ ተቃውሞውን ወደ ኢህአዴግ መንግስት ካዞረ በሁዋላ፣ ገዢው ፓርቲ ተቃውሞውን ያስነሳው በአገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ
የሚታገለው ሰማያዊ ፓርቲ ነው በማለት የከፈተው ሰፊና አሰልቺ ፕሮፖጋንዳ የህዝቡን አመለካከት ሊቀይር አለመቻሉ ከፍተኛ ካድሬዎችን ስጋት ላይ ጥሎአቸዋል፡፡
በመስቀል አደባባይ የታየውን ህዝባዊ ቁጣ  ሰማያዊ ፓርቲ የቀሰቀሰው የመንደር ሁከት ለማስመሰል በስሩ በሚገኙ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን በተደጋጋሚ ፕሮፖጋንዳ የሰራ ቢሆንም ፣ ፕሮፓጋንዳው ሕዝቡን ብቻ ሳይሆን የራሱን አባሎች ማሳመን አለመቻሉ ከፍተኛ
ካድሬዎችን ድንጋጤ ላይ ጥሎአቸዋል።
በአዲስአበባ አስተዳደር በተለያዩ የመንግስት ቢሮዎች  ይህንኑ የሕዝብ ተቃውሞ በማስመልከት ሰማያዊ ፓርቲ ያቀነባበረው መሆኑን በመግለጽ ሁኔታውን ለማውገዝ ታስቦ ሰሞኑን ተከታታይ ስብሰባዎች የተካሄዱ ቢሆንም አጥጋቢ ውጤት ሊገኝባቸው አልቻለም፡፡
በተለይ የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎች ጭምር ፍረጃው አሳማኝ አለመሆኑን በመጥቀስ ሕዝቡ በተለይ በመልካም አስተዳደርና በኑሮ ውድነት ችግሮች ውስጥ ሆኖ መቃወሙ የሚጠበቅ እንደነበር፣ ከሰማያዊ ፓርቲ ይልቅ ወደውስጣችን በመመልከት ችግሩን ካልቀረፍን
ከዚህም የባሰ ችግር ሊገጥመን ይችላል በሚል የተንጸባረቁ ደፈር ያሉ አስተያየቶች ያልተጠበቁ በመሆናቸው የመድረክ መሪ ካድሬዎችን ጭምር አስደንግጦአል፡፡

Monday, April 27, 2015

በስደት በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸሙትን አሰቃቂ ድርጊቶች የሚያወግዙ ሰልፎችንና የሻማ ማብራት ስነስርአቶች ተካሄዱ

ሚያዝያ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባሳለፍነው ሳምንት በሊቢያ፣ በደቡብ አፍሪካና በየመን በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የደረሰውን አሰቃቂ ግፍ የሚቃወሙ ሰልፎች፣ የሻማ ማብራት ስነስርአቶችና ጸሎቶች በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በእስያና
በአውስትራሊያ ተካሂዷል። በለንደን ሰኞ ሚያዚያ 19 ቀን 2007 ዓም በተካሄደው ከፍተኛ ተቃውሞ ኢትዮጵያውያን በወገኖቻቸው ላይ የደረሱትን በደሎች አጥብቀው ኮንነዋል። ጋዜጠኛ ወንድማገኝ ጋሹ በስፍራው ተገኝቶ እንዳለው እስከ አንድ ሺ የሚጠጉ
ኢትዮጵያውያን ከትራፋልጋር ስኩየር በመነሳት ወደ እንግሊዝ ፓርላማ አምርተዋል። በኒዉዚላንድ ኦክላንድ  የኢትዮጵያ ትንሳኤ መወያያ መድረክ ባዘጋጀዉ የሻማ ሥነስርዓት ላይ ኢትዮጵያኑ የሻማ ማብራት ሥርዓት  አካሒደዋል፡ ፡
በጃፓን ቶክዮ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም በደቡብ አፍሪካ ኢምባሲ ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል።
በስዊዘርላንድ ጄኔቫ፣ በዙሪክ፣ በርን፣ ሴንት ጋለን፣ ባዝል፣በፈረንሳይ ፓሪስ፣ በሆላንድ አምስተርዳም፣ በአውስትራሊያ ፐርዝ ፣ በጀርመን ፍራንክፈርት ፣ በሉክሰንበርግ ፣በኖርዌይ አስሎ፡በግሪክየህሊና ጸሎት ተካሂዷል።
በሌላ በኩል ደግሞ መንግስት በሊቢያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በግብጽ እና በካይሮ በኩል ለማውጣት እንቅስቃሴ መጀመሩን ቢያስታውቅም፣ ወደ አገራቸው መመለስ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ትሪፖሊ ለሚገኘው የመንግስት ተወካይ ስልክ ደውለው ምላሽ
ማጣታቸውን ተናግረዋል። ግብጽ የሚገኘው ኢምባሲ የሚሰጠው የስልክ ቁጥር አይሰራም በማለት አቤቱታ እያቀረቡ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ የተካሄደውን የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ በቁጥጥር ስር ውለው ከነበሩት ከ1 ሺ በላይ ወጣቶች፣ አብዛኞቹ ተፈትው ከ150 ያላነሱት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፖሊስ አስታውቋል።
ፖሊስ ተቃውሞውን ያስነሱት ሰማያዊ ፓርቲና አንድነት ፓርቲዎች ናቸው ብሎአል። ሰማያዊ ፓርቲ የመንግስትን ክስ  ወዲያው ውድቅ ሲያደርገው፣ አዲሱ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ትዕግስቱ አወሉ አንዳንድ አባሎቻችን ከእኛ እውቅና ውጪ ሰልፍ ላይ
ተገኝተዋል ብለዋል።  አቶ ትእግስቱ 1 የብሔራዊ ም/ቤት አባላችንና ሌላ 1 ጸሃፊ ሰልፉ ላይ መገኘታቸውን ከፖሊስ የምርመራ ሪፖርት ላይ ተመልክቻለሁ ብለዋል። የአቶ ትእግስቱ ንግግር በኤፍ ሬዲዮኖች እንዲራገብ የተደረገ ሲሆን፣ ንግግሩ ብዙ የአዲስ አበባ
ነዋሪዎችን ማበሳጨቱ ታውቋል።
አዲሱ የአንድነት ፓርቲ የኢህአዴግ ተለጣፊ መሆኑን ከዚህ በላይ ማሳያ የለም በማለት የህዝብ አስተያየት በማሳባሰብ ዘጋቢያችን በላከው መረጃ ላይ ጠቅሷል።

Friday, April 10, 2015

The ruling Ethiopian People Revolutionary Democratic Front (EPRDF), which came to power in 1991 after a guerilla war against the bloody Mengistu Haille Mariam regime, holds total political sway. The coalition, which consists of four political parties, holds 499 out of the 547 national assembly seats.
To illustrate the country’s political intolerance, the government often refers to the opposition in derogatory terms like “chauvinists”, “narrow nationalists”, “secessionists” or simply “enemies”.
The Ethiopian government controls all spheres of life, from media to people’s daily lives. The main national broadcaster, Ethiopian Television, and most of the 10 radio stations, are owned by the government. Introduced in 1992 and giving the police sweeping powers to detain journalists without trial and shut down dissenting media outlets, Ethiopian media laws make the National Security (Amendment) Bill 2014 look like a legal walk in the park.
The ruling Ethiopian People Revolutionary Democratic Front (EPRDF), which came to power in 1991 after a guerilla war against the bloody Mengistu Haille Mariam regime, holds total political sway. The coalition, which consists of four...
ECADFORUM.COM
Like · Comment ·